Saturday, October 26, 2013

‘ወደፊት እያሰብን ወደኋላ መሮጥ ተገቢ አይደለም። በመጣንበት መንገድ ብንመለስ፣ የተነሳንበት ቦታ ላይ ነው መልሰን የምንደርሰው። ‘ http://sebhatamare.files.wordpress.com/2013/10/entc3.jpg

ስብሃት ህወሃት ጠቦ ታሪኩን እንደሚቋጭ አረጋገጡ

ህወሃትን ገልብጦ “ከየትኛው ክልል ድጋፍ ሊገኝ?”
sebhat nega
ስብሃት ነጋ የኢህአዴግ አባትና ፈጣሪ የሆነው ህወሃት የመጨረሻው ታሪኩ ጠቦ እንደሚቋጭ ይፋ አደረጉ። ችግር የህወሃት ልዩ በረከትና ስጦታ እንደሆነ በማመልከት ህወሃት ውስጥ ልዩነትና መፈርከስ አደጋ ተከስቶ እንደማያውቅ ሸመጠጡ።

በኢትዮጵያ ከግማሽ ክ/ዘመን በላይ የቆየማንዴላን የተመለከተ የደህንነት ሚስጥር ዛሬ ይፋ ሆነ።ሚስጥሩን ማንዴላም እስካሁን ድረስ አይውቁትም።

ኔልሰን ማንዴላ እና ጄኔራል ታደሰ(የማንዴላ አሰልጣኝ በወቅቱ ኮ/ል የነበሩ)ኮልፌ ፖሊስ ማሰልጠኛ
ኔልሰን ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ የፀረ-አፓርታይድ (የዘር-መድሎ) ተዋጊ አርበኛ መሆናቸው ይታወቃል።ለእስር የተዳረጉት ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና ወስደው እንደተመለሱ ነበር። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ 1962 ዓም ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው በወቅቱ ለማንዴላ ኢትዮጵያ ፓስፖርት በመስጠት አጋርነቷን የገለፀች ብቸኛ ሀገር ነበረች።
ከዘመናት በኃላ ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ወቅት  የግድያ ሙከራ ተደርጎ እንደነበር ሚስጥሩን ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ ይዘው የቆዩ በቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ዘመን የኢትዮጵያ ፖሊስ መኮንን ዛሬ ጥቅምት 15/2006 ዓም ለመጀመርያ ጊዜ በሸገር ራድዮ የዜና እወጃ ላይ ገልፀዋል።
ሻምበል ጉታ ዲንቃ በንጉሡ ዘመን የፖሊስ መኮንን ነበሩ። ማንዴላን በከፍተኛ ሚስጥር እንዲጠብቁ ኃላፊነት ከተሰጣቸው ጄኔራል ታደሰ(የማንዴላ አሰልጣኝ በወቅቱ ኮ/ል የነበሩ)፣ኮ/ል ፍቃደ እና ሻምበል ፈቃደ ውስጥ ነበሩ።ዛሬ የ76 አምቱ የእድሜ ባለፀጋ  ሻምበል ጉታ ዲንቃ ለሸገር ሲናገሩ እንዲህ አሉ።
” ማንዴላን እንድጠብቅ ኃላፊነት የተሰጠኝ እኔ ነበርኩ።ማንዴላ የሚያድሩበት እና ወታደራዊ

ሰንደቅ አላማውን ያዋረደው ማን ነው? ጌታቸው ሺፈራው

 ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ ‹‹መንግስት በእምነታችን ጣልቃ እየገባ ነው!›› በሚል ከአንድ አመት በላይ እየተቃወሙ የቀጠሉት የእስልምና እምነት ተከታዮች ሀምሌ 19/2005 ዓ/ም ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ ኢህአዴግ ‹‹ሰልፈኞቹ የሰንደቅ አላማውን ክብር አዋርደዋል?›› የሚል ክስ ማቅረቡ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ የተበጣጠሰውን ሰንደቅ አላማው የያዙት ሰልፈኞቹን የሚኮንን መንግስት ቅጥረኞችም ይሁን ሰልፈኞቹ ትክክል ነው ብዬ አላምንም፡፡ ምንም እንኳ ህግ የማስከበር ሀላፊነት የነበረበት ቢሆንም ኢህአዴግ ጉዳዩን ያነሳው በእርግጥም በሰንደቅ አላማ ክብር ስለሚያምን አይደለም፡፡ የዚህ ጽሁፍ አላማም ሀምሌ 19/2005 ዓ/ም የተፈጠረው ስህተትን ማስተባበል አሊያም መክሰስ ሳይሆን በተፈጠረው ክስተት ‹‹ሌሎችን›› የሚከሰው ኢህአዴግ ራሱ ሰንደቅ አላማውን እያዋረደ መቀጠሉን የተለያዩ ክስተቶችንና የራሴን ገጠመኝ በመቃኘት ማሳየት ነው፡፡

Thursday, October 24, 2013

Jawar Mohammed on ESAT

October 24, 2013Dear ESAT Producer of “Sile Ethiopia”,
I followed today, Oct. 22 , program of “Sile Ethiopia”. The “denouncement”, by Jawar Mohamed on his facebook about the recent woyane appointment of high rank military officials which you read, is not unexpected. Jawar, the leader of “Oromo First” movement, is seeing all the politics from Oromos VS Others angle.
He publicly supported OPDO even if it is a Woyane creation to control the “Oromo Kill”. He criticized Woyane for not appointing Oromo for top military position but he is behind OPDO for cleansing other ethnicity from Oromo Kilil.
Jawar Mohamed is a strategic ally of Woyane. He seems to quarrel here and there with Woyane like he has done this week with the appointment of high rank military officials. Strategically he is a promoter of Woyane divide and rule by ethnicity.
You are trying to bring back Jawar Mohamed into ESAT after he was rejected by Ethiopians following “Ethiopia out of Oromia” and “Slit the non Oromos throat” rant few months back.
Jawar Mohammed and Woyane are not different. Both are driven by ethnicity. The difference is Woyane on power while Jawar and the “Oromo First” are conspiring against Ethiopia and Ethiopians from Diaspora. We should not waste precious airtime promoting such divisive individual.
Thanks,
Tedla Asfaw.

Who’s Having “Nightmares” in Africa?

October 24, 2013by Alemayehu G. Mariam

Great African leaders have dreams. The rest have nightmares.

Just last month, Kenyatta loudly proclaimed his innocence at a graduation ceremony
President Kenyatta, left, with Deputy President Ruto, Nairobi, Kenya, Oct. 12, 2013.
Recently, African leaders, at least those at the helm of the African Union and their flunkies, have been reporting endlessly recurring ghastly nightmares of Lady Justice “race hunting” them with scales in one hand and a sword in the other. President Uhuru Kenyatta, described by Time Magazine as “Kenya’s richest man”, last week vividly described  his sleepless nights interrupted by nightmarish naps to his brethren at the African Union:

ሕዝባዊ እምቢተኝነት በውጭ አገር፤ እንዴት?


ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሁለገብ ትግል ወያኔ ማስወገድ ይገባል ብሎ የሚያምና ለዚህም የሚታገል ድርጅት ነው። “ሁለገብ ትግል” ሲባል ሰላማዊም ሰላማዊ ያልሆኑም የትግል ስልቶችን መጠቀም ማለት ነው። “ሁለገብ ትግል” ሲባል በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም የሚደረጉ ትግሎች ማለት ነው።

ከዚህ አንፃር በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሚና ምን ሊሆን ይገባል?
በግንቦት 7 እምነት በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በድጋፍ ሰጭነት ሳይወሰኑ የትግሉ ቀጥተኛ ተሳታፊዎች መሆን ይኖርባቸዋል። በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በወያኔ ጥቅሞችና ተቋማት ላይ በማመጽ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን አርዓያ መሆን ይኖርባቸዋል።
በዚህ ረገድ የተጀመሩ አበረታች ጥረቶች አሉ፤ ለምሳሌ:

Ethiopians in Norway vowed to stand beside Ginbot 7 popular force


123 
On 28th of September 2013, successful fundraising was conducted for Ginbot 7 Popular Force (G7pf), recently established and struggling against the woyane junta. The fundraising event, staged from 4:00 – 12:00 p.m. local time, was coordinated by a taskforce established by Democratic Change in Ethiopia Support Organization in Norway (DCESON). The event was able to attract many participants from all over Norway and other European countries. The event was one of the success stories in the history of fundraising in terms of both participation and raised amount of money.

በቤይሩት ኢትዮጵያዊቷ በመኪና አደጋ ህይወትዋ አለፈ

በቤይሩት ኢትዮጵያዊቷ በመኪና አደጋ ደርሶባት ቆንስላ ጽፈት ቤቱ ሀላፊነት አልወስድም በማለቱ መዳን ስትችል ህክምና ባለማግኘቷ ለህልፍት በቃች…
የቆንስላ ጽፈት ቤቱ ሀላፊዎች በእህቶቻችንን ላይ የሚደርሰውን ግፍና መከራ ችላ በማለት የራሳቸውን ብቻ ቢዝነስ ሲያሳዱ የበርካቶች ህይወት እንደቀልድ ያልፋል: : ፥ ቤተሰቦቻቸው ተበድረው የላኳቸው ሊጆቻቸውን እሬሳ እንደገና በብድር ሲያስገቡት ብታዮ ልብ ይሰብራል:: ከዚህ በላይ በዜጎቹ ላይ ቁማር የሚጫወት የዜጎቹ መከራ ግፍ ስካይና ጉዳት የማያሳስበው መንግስት በሀለም ላይ አለ ?.ከልብ ሀዘን ተሰምቶናል ቆንስላው ስራው ምን ይሆን? መንግስት ስራው ምን ይሆን?
11

የአሲምባ ፍቅር (ክፍል ሁለት)

October 24, 2013የአሲምባ ፍቅር
ደራሲ- ካህሳይ አብርሀ (አማኑኤል)
ትችት-(ሐተታ)- ሽፈራው
Assimba.org web site ethiopian information
አንባቢ ሆይ : በክፍል አንድ ባጭሩ አንደገለፀሁት ጓድ “አማኑኤል” ጋር በሕብረ ብሔራዊዉ የኢትዮጵያ ህዝባዊዉ አቢዮታዊዉ ሠራዊት (ኢሕአሠ) በወሎ፣ በቤጌምድር እና በትግራይ በብዙ ፈተናና ችግር አብረን ተካፍለናል። ከ30 አመት በኋላም ተገናኝተን ስለ ኢሕአሠ መጽሃፍ ለመጻፍ እንዳሰበ ሲነግረኝ እንደምረዳዉ ቃሌን ሰጥቸ በሰፊው አስተዋጽዖ አድርጌአለሁ ።

ፋሺሽቶች በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸሙት ግፍና ስለሚጠበቀው ፍትሕ በዳላስ ከተማ የተከናወነ ውይይት

October 24, 2013
  • የውይይቱ አስተናባሪ፤ አቶ ይልማ ዘርይሁን፤ በዳላስ የኢትዮጵያውያን መረዳጃ ማሕበር ሬዲዮ ያቀረቡት መግለጫ፤
  • ፋሺሽቶች በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸሙት የጦር ወንጀል፤ ሁለት ኢጣልያውያን ፊልም እያዘገጁ ነው።
የዳላስ/ፎርት ወርዝ የኢትዮጵያውያን የጋራ መረዳጃ ማሕበር እና ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ GLOBAL ALLIANCE FOR JUSTICE: THE ETHIOPIAN CAUSE (www.globalallianceforethiopia.org) ፋሽስት ኢጣልያኖች በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸሙት ግፍና ስለሚያስፈልገው ፍትሕ እንዲሁም ስለ ጉዳዩ በዶክመንታሪ መልክ ስለሚዘጋጀው ፊልም፤ ኤል.ቢ.ጄና ኮይት ላይ በሚገኘው ግራንድ ሆቴል፤ ቅዳሜ፤ October 19, 2013፣ ከሰዓት በኋላ 3:00 pm እስከ 6 ፒ. ኤም
ተከናውኗል።
[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

ዳግም በሀገር ፍቅር ስሜት ያስተሳሰሩን ዋልያዎቹ

October 24, 2013በፍቅር ለይኩን
The Ethiopia national football team
‹‹ሀገሬ ናይጄሪያ ኢትዮጵያን ለማሸነፍ ምትችልበት ብቸኛው መንገድ አንድም ጸሎት አሊያም ዕድል ነው፡፡›› የቀድሞው ዝነኛውና ኮከብ የናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች የሆነው ካኑ ለአንድ ታዋቂ የስፖርት ድረ ገጽ በሰጠው አስተያየት ነበር እንዲህ ያለው፡፡ በጨዋታው ላይ የሆነው ሁሉ እንዳለ ሆኖ በእውነትም ካኑ እንደገመተው የናይጄሪያዎቹ ፈጣን ንስሮች ‹‹በጸሎትም ወይም በዕድል›› ሊባል በሚችል ሁኔታ የኢትዮጵያ አቻዎቻቸውን 2-1 በማሸነፍ ለ2014 የብራዚሉ የዓለም ዋንጫ ብሩህ ተስፋን የሰነቁና መንገዱን ያስተካከሉ መስለዋል፡፡

ሁሉም ይናገር ሁሉም ይደመጥ!! (ከአንተነህ መርዕድ እምሩ ቶሮንቶ)

October 24, 2013ከአንተነህ መርዕድ እምሩ ቶሮንቶ
በቶሮንቶና ባካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለፈው እሁድ ኦክቶበር 13 ቀን 2013 ዓ ም ለሶስተኛ ጊዜ በደማቅ ሁኔታ በመሰባሰብ ኢሳትን የሚያጠናክር የገንዘብና ልዩ ልዩ ድጋፍ አድርገዋል። ወያኔ ከአገር አልፎ ውጭም የፈጠረውን ጊዜያዊ ፍርሃት ሰብሮ፣ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲሰፍን የሚደረገውን ትግል ሁሉ ከወያኔ ባልተናነሰ በማደናቀፉ እርኩስ ተግባር የተካኑ የጨለማ ውስጥ ወገኖችም የፈጠሩትን አሉባልታ ከምንም ሳይቆጥር የመጣው ኢትዮጵያዊ ለአገሩ ነፃነት ማንኛውንም መስዋዕት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ያረጋገጠበት ነበር። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]
ESAT Toronto report
ESAT Toronto report, Abebe Gellaw, Berhanu Nega

ጫልቱ እንደ ሄለን ከቡርቃ ዝምታ የቀጠለው መርዛማ ብዕር

October 24, 2013ዳኛቸው ቢያድግልኝ
ተራሮች አንቀጠቀጥኩ ያለው ትውልድ አካል ነኝ ባዩ ወንድማችን በቡርቃ ዝምታው በማር የተለወሰ መርዝ አሰናድቶ አማራና ኦሮሞ ሲተራረድ ዙርያ ከበው በለው! አትማረው! የሚሉትን የአባቱን ሀገር ፖለቲከኞች አስቦ የጻፈው ክታብ መሆኑ ተነግሮ አብቅቶለታል። ተስፋዬ የጦር ሜዳ ዘጋቢነቱን በኢትዮጵያውያን ተምሮ ኢትዮጵያዊ አይደለንም ብለው ለሚወጉን ማገልገሉና በደል መፈጸሙ እውነት ነው። ለዚህ ውለታውም የዘመናት ታሪክ ያለውን ድርጅት ያለምንም ክህሎት በአዛዥነት ይዞ እንዳሻው እንዲፈነጭበት ተሰጥቶት ነበር። ቁንጮ ሆኖም የሚበቃውን መረጃ ከክምችቱ እንዲያገኝ ሆኖ መሰየሙንና ክምችቱንም ለፕሮፓጋንዳ መሳርያነት እንዲጠቀምበት ሙሉ መብት ተሰጥቶት እንደነበረም እናውቃለን። ተስፋዬ አገር የለቀቀበትን ጊዜ መለስ ብለን ብንመለከት ለሻዕብያ ያለው ቅርበት ከወያኔ ጋር ለመቀያየም ምክንያቱ መሆኑን መገመት ይቻላል። በተስፋዬ ስራዎች ውስጥ የኤርትራ ጉዳይ ልዩ ቦታ እንዳለውና ከጻፈም ጀግና ብልህና አስተዋይ እንደሚያደርጋቸው የታወቀ ነው።Tesfaye Gebreab's New Book: “Yesidetegnaw Mastawesha

ወያኔ ወደ ሙኒክ መጥቷልና ወገን ተዘጋጅ!!!!!!!!!

October 24, 2013ወያኔን መደገፍ ማለት በወገኖችዎ ላይ የሚደርሰውን ይህን ግፍ መደገፍ መሆኑን ይገንዘቡ!!
Ethiopia 1997
የወያኔን የዘረፋ ጉዞ ተባብረን እንግታ!!
የወያኔ ቁንጮ የነበረው መለስ ዜናዊ ከሚስቱ ጋር በመሆን ከዘረፉት በላይ ለመዝረፍ በነደፉት የአባይ ግድብ እቅድ ሳቢያ በውጭ ሃገር ካለው ወገናችን ጉልበት በዝባዥ የሆነውን የፈረንጅ ሃገር ስራ ተጋትሮ ያገኛትን ለመመንተፍ የመለስ ውሾች የሆኑት ካድሬ ተብዬዎች ላይ ታች ሲንጠራወዙ ሁለት ዓመት ሆናቸው። ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያንም እነዚህን ተላላኪ አሽከሮች በየደረሱበት እያሳደዱ ስብሰባ ብለው የጠሩትን ሲያከሽፉ፣ እግሬ አውጭኝ ሲያስሸመጥጡ፣ የእነርሱን ባንዲራ እያነሱ እውነተኛ የኢትዮጵያ ባንዲራ ሲሰቅሉ፣ ወያኔዎቹ የተከራዩትን አራሽ ተቆጣጥረው የራሳቸውን ስብሰባ ሲያካሄዱ፣ ወዘተ ወዘተ ብዙ ገድል አይተናል። ካድሬዎቹ ውሾች ግን ወትሮም የሰውነት ክብር የላቸውምና በደረሰባቸው ተደጋጋሚ ውርደት ተሸማቀው አርፈው አልተቀመጡም።

Tuesday, October 22, 2013

የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ እና አስተያየት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ለአሥር ቀናት በመላ ሀገሪቱ እና ከሀገር ዉጪ የሚገኙ አብያተክርስቲያናት ተወካዮች በተገኙበት የሀገረ ስብከቱን ጳጳሳት ጠርታ በውስጧ ስላሉ ችግሮች አወያይታለች።
Autor: Ludger Schadomsky
Copyright: Ludger Schadomsky/DW
Titel: Sitz des Patriarchen der äthiopisch-orthodoxen Kirche in Addis Abeba 
Thema: Alle vier großen Religionsgemeinschaften Äthiopiens - Orthodoxe und katholische Christen, Protestanten und Muslime - haben im Vorfeld der Wahl in einem gemeinsamen Appell für einen friedlichen Wahlgang geworben. Die beiden Tauben vor dem Sitz des Abuna, des Patriarchen der Orthodoxie Äthiopiens, stehen dafür sinnbildlich. 
Schlagwörter: Orthodoxie Äthiopien, Abuna Paulos, Dialog der Religionen, Wahl Äthiopien 2010, Elections Ethiopia 2010
በጉባዔው ለችግሮቹ መፍትሔ ለማፈላለግ የተደረሰውን ስምምነት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶሱ በፓትሪያርኩ ሰብሳቢነት ዛሬ ጠዋት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ከቤተ ክርስትያኒቱ ምሁራን አንዱ የሆኑት በቅድሥት ሥላሤ መንፈሣዊ ኮሌጅ የሚያገለግሉት ሊቀ ማዕምራን መምህር ደጉ ዓለም ጉባዔው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች መልካም መሆናቸውን ቢናገሩም፣ በተግባር መተርጎማቸውን እንደሚጠራጠሩት ገልጸዋል ።

የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ እና አስተያየት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ለአሥር ቀናት በመላ ሀገሪቱ እና ከሀገር ዉጪ የሚገኙ አብያተክርስቲያናት ተወካዮች በተገኙበት የሀገረ ስብከቱን ጳጳሳት ጠርታ በውስጧ ስላሉ ችግሮች አወያይታለች።
Autor: Ludger Schadomsky
Copyright: Ludger Schadomsky/DW
Titel: Sitz des Patriarchen der äthiopisch-orthodoxen Kirche in Addis Abeba 
Thema: Alle vier großen Religionsgemeinschaften Äthiopiens - Orthodoxe und katholische Christen, Protestanten und Muslime - haben im Vorfeld der Wahl in einem gemeinsamen Appell für einen friedlichen Wahlgang geworben. Die beiden Tauben vor dem Sitz des Abuna, des Patriarchen der Orthodoxie Äthiopiens, stehen dafür sinnbildlich. 
Schlagwörter: Orthodoxie Äthiopien, Abuna Paulos, Dialog der Religionen, Wahl Äthiopien 2010, Elections Ethiopia 2010
በጉባዔው ለችግሮቹ መፍትሔ ለማፈላለግ የተደረሰውን ስምምነት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶሱ በፓትሪያርኩ ሰብሳቢነት ዛሬ ጠዋት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ከቤተ ክርስትያኒቱ ምሁራን አንዱ የሆኑት በቅድሥት ሥላሤ መንፈሣዊ ኮሌጅ የሚያገለግሉት ሊቀ ማዕምራን መምህር ደጉ ዓለም ጉባዔው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች መልካም መሆናቸውን ቢናገሩም፣ በተግባር መተርጎማቸውን እንደሚጠራጠሩት ገልጸዋል ።

የስዊድን የጦር ኮሚሽን በኦጋዴን ስለተፈጸመው ወንጀል አፋጣኝ መልስ እንደሚሰጥ አስታወቀ

ኢሳት ዜና :-በኦጋዴን የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰትና የጦር ወንጀል የሚያሳየው ዘጋቢ ፊልም በቅርቡ በስዊድን ቴሌቪዥን መለቀቁን ተከትሎ ዛሬ አርብ፣ የስዊድን የጦር ኮሚሽን ማስረጃዎችን ተረክቧል።
ማስረጃዎችን ለኮሚሽኑ ያስረከቡት ሂደቱ ዋና ተወናይ የሆነው ወጣት አብዱላሂ የሱፍና የአለማቀፍ የህግ ባለሙያዎች ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ስቴላ ጋርደ ናቸው።

የጦር ኮሚሽኑ የቀረበለትን ማስረጃ በማየት አፋጣኝ ውሳኔ እንደሚሰጥ መግለጹን ወጣት አብዱላሂ ለኢሳት ተናግሯል።
ይህ በእንዲህ እንደላ በስልጣን ላይ የሚገኙ የአፍሪካ መሪዎች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲከበር  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጠየቁ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም የአፍሪካ ህብረት 15ኛው አስቸኳይ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በጉዳዩ ላይ በመምከር ያስተላለፈው ውሳኔም ተግባራዊ እንዲደረግ ጠይቀዋል።


ዶክተር ቴዎድሮስ  ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ከሆኑ የዓለም አቀፉ የፀጥታው ምክር ቤት አባል ሀገራት አምባሳደሮች ጋር ባደረጉት ውይይት አለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት  የፊታችን የፈረንጆች ህዳር 12 ቀን የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታንና ምክትላቸውን ዊሊያም ሩቶን ለመክሰስ የያዘውን እቅድ መሰረዝ አለበት በማለት መናገራቸውን የጊዜው ፓርቲ ልሳን ፋና ዘግቧል።
በውይይቱ ላይ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ያላቸው አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ሩሲያ፣ ቻይናና ፈረንሳይን ጨምሮ የ10 ቋሚ ያልሆነ መቀመጫ ያላቸው አባል ሀገራት አምባሳደሮች ተሳትፈዋል።


ታዋቂው ደቡብ አፍሪካዊ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሊቀጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ የአፍሪካ መሪዎች በፍርድ ቤቱ ላይ የሚያሰሙት ተቃውሞ ” እንደፈለጉ ሲግድሉና ሲያሰቃዩ እንዳይጠየቁ ነው” ብለዋል።
የቀድሞው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ በበኩላቸው ፣ ጥያቄውን ያቀረቡትን “ማፈሪያዎች” ብለዋቸዋል።
ዶ/ር ቴዎድሮስ ያቀረቡት ጥያቄ የኢህአዴግ ባለስልጣናት በፍርድ ቤቱ እንቅስቃሴ ስጋት ላይ እየወደቁ መምጣታቸውን የሚያሳይ ነው።

Zimbabwe arrests 38 Ethiopian

Zimbabwe has arrested 38 Ethiopians trying to cross into South Africa through an illegal crossing.
Beitbridge in Zimbabwe which is at the border with South Africa. 38 illegal Ethiopian immigrants were arrested here as they attempted to cross to South Africa. The crew of the bus that was carrying them, which is owned by an influential member of President Robert Mugabe’s Zanu PF was also detained. GOOGLE MAPS
Zimbabwe has arrested 38 Ethiopians who were trying to cross into South Africa through an illegal crossing point. According to police the group that had hired a bus from the eastern city of Mutare – at the border with Mozambique – were intercepted in Beitbridge as they prepared to cross into South Africa. The suspects aged between 20 and 30 had also reportedly used an illegal entry point to enter Zimbabwe from Mozambique. Beitbridge police commander Chief Superitendent Lawrence Chinhengo said police investigations were on-going and the group had been charged for illegal entry. “We have had a number of such cases where these illegal immigrants come into the country through Mutare,” he told state media on Tuesday. “We are not leaving any stone unturned, we want to get to the bottom of this syndicate.” He said the crew of the bus that was carrying the suspects, which is owned by an influential member of President Robert Mugabe’s Zanu PF had also been detained.
TIP-OFF


“We received a tip-off that there were 38 Ethiopians who were being transported aboard a Senator Express bus from Mutare. We then teamed up with the Department of Immigration,” Chief Superintendent Chinhengo said. “We will not tolerate such lawlessness where people go to the extent of hiring buses to facilitate illegal immigration.” Zimbabwe is used by traffickers as a key route because of its porous Beitbridge border with South Africa. Syndicates help thousands of people every month to sneak into Africa’s biggest economy. South Africa is home to over three million Zimbabweans, most of them illegal immigrants.Thousands are sent back home every year but they quickly find their way back to South Africa using the illegal entry points.
Refugees from Ethiopia, Eritrea and the Democratic Republic of Congo also use Beitbridge, the largest inland port in Southern Africa, to sneak into South Africa.
About these ads .
ታዋቂው ብሎገር አብረሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው በትግራይ ክልል ክልተ አውላዕሎ ወረዳ (ጣብያ አይናለም) በቤተክርስትያን ግንባታ ምክንያት በህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል አምባጓሮ ተፈጥሮ አንድ ቄስ ተገደሉ።More...
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/8586
ታዋቂው ብሎገር አብረሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው በትግራይ ክልል ክልተ አውላዕሎ ወረዳ (ጣብያ አይናለም) በቤተክርስትያን ግንባታ ምክንያት በህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል አምባጓሮ ተፈጥሮ አንድ ቄስ ተገደሉ።More...
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/8586
(ፍኖተ ነፃነት) 33 ፓርቲዎች እየተባሉ የሚጠሩት በ15/02/ 05 የአዳማ ፔቲሽን ተብሎ የሚጠራውን የፈረሙ ናቸው፡፡ የጋራ ስምምነት ሰነድ የፈረሙት 24 ፓርቲዎች ሲሆኑ ጥቅምት 10 ቀን በዋለው ስብሰባቸው ወደ ቅንጅት አድገዋል፡፡More...
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/8584

ሌባ ተይዞ ዱላ ይጠየቃል? በሆላንድ

መስፍን ወልደ ማርያም
ጥቅምት 2006
በአሥራ አምስተኛው  ምዕተ-ዓመት ግድም ሆላንድ የታወቀ የባሕር ኃይል ሆኖ ከደቡብ አፍሪካ እስከደቡብ አሜሪካ፣ የኔዘርላንድ የቆዳ ስፋት 41 526 ኪሜ ካሬ ወይም የትግራይ ግማሽ ነው፤ የሕዝቡም ቁጥር አሥራ ስድስት ሚልዮን ተኩል አይሞላም፤ የትግራይን ግማሽ በሚሆን መሬት ላይ የትግራይን ሦስት እጥፍ ግድም የሚያህሉ ሰዎች ይኖሩበታል፤ ሆኖም ጥንት ከደቡብ አፍሪካ እሰከደቡብ አሜሪካ፣ በእስያም ኢንዶኒዝያ ላይ የቅኝ ግዛት የዘረጋ ትንሽ አገር ነበር፤ አሁንም ትንሽ አገር ነው፤ አሁንም ሀብታም አገር ነው፤ ዋናው ሀብቱ ሕዝቡ ነው፤ አሥራ አምስት ሚልዮን ግድም የሚሆን ሕዝብ ከባሕር ጋር እየታገለ ያገኘውን መሬት ይዞ እንዲህ ያለ ሀብታም መሆኑን ሳይ እኛ በጣም ሰፊ መሬትና ስድስት ጊዜ ያህል ከኔዘርላንድ የሚበዛ ሕዝብ እያለን ቆሞ-ቀር ብቻ

BREAKING: Last week terrorist bomb explosion in Ethiopia was planted by the regime – witnesses

EthiopianReview.com | October 22nd, 2013
Ethiopian Review has confirmed from multiple witnesses that the Oct. 13, 2013, alleged terrorist bomb explosion in Ethiopia’s capital Addis Ababa was planted by the regime.
addis ababa terrorist explosionAccording to our sources, the night before the explosion, two dead bodies were taken by TPLF security agents from Menilik Hospital and placed inside the house where the explosion took place. The house was allegedly rented by Somali nationals, but it has now been exposed that the Somalis were brought from the Somali region by the regime’s security agents a few days before the incident took place and were transported back right after the explosion.
Ethiopian Review’s investigation has uncovered that the Somali nationals were brought to Addis Ababa by a special unit named 03 within the TPLF (ruling party) security apparatus that is under the direct command of Debretsion Gebremichael and Getachew Assefa, members of the TPLF politburo.
Contacted by Ethiopian Review, officials at the local police station have said that they are not part of the investigation and do not know the identities of any of the individuals, including the owners of the house who are allegedly involved. But according to residents in the neighborhood, the house belongs to well-known TPLF supporters who are suspected by every one of being spies.
The regime has so far not been willing to reveal the true identities of those who have reportedly been killed while setting up the bomb.
This is not the first time that the TPLF junta has exploded bombs and blamed it on its enemies. A diplomatic dispatch sent to Washington DC by American diplomats in Addis Ababa confirms (in a Wikileaks release) that the regime in Ethiopia is known to fabricate bombing incidents.
It needs also to be noted that the TPLF junta is one of the major sources of weapons to the Al Shabab terrorist group, according to South African Ambassador to the United Nations, Dumisani Kumalo, who was serving as chairman of the U.N. Security Council’s Somalia sanctions committee [read here].
Al Shabab itself is the creation of the TPLF junta. Without the invasion of Somalia by TPLF, Al Shabab would not have come into existence.

Are Oromos Singled Out and Disproportionately Tortured in Ethiopia?

torture4_OromoOctober 21, 2013 (Oromo Press) — You may ask people in Oromia, what is the language most widely spoken in Ethiopia’s prisons? Who are the ethnic groups singled out and subjected to extreme torture in Ethiopia’s notorious torture facilities? The answers to both questions are Afan Oromo (the Oromo language), and Oromo people respectively. People have pointed to this time and again to the point that torture and political imprisonments are almost becoming synonymous with one ethnicity in Ethiopia, the Oromo people.
Human Rights Watch just released a riveting account of torture in Maekelawi (comparable to Auschwitz of the Nazi era  and Gitmo of the post-9/11 period). The conditions Oromo political prisoners, including school children, who have barely come of age, face in Maekelawi and Kaliti and other facilities of torture is similar to those faced by the Jewish community during the Holocaust. The comparison to Gitmo might be a little far-fetched since Oromo detainees are innocent and unarmed civilians who get thrown into torture prisons in most cases for no other valid reasons than their default belonging in a nationality group that is different, politicized and competing with the nationality group that controls the levers of power through totalitarian parties known as the Tigire Peoples Liberation Front/ The Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Front.
I often get asked by Faranjii sympathizers with the Oromo conditions questions such as: did anybody try to sneak cameras into prisons and expose the tortures? Did anyone interview survivors of torture and human rights abuses and archive the information? When it comes to the Oromos doing the work by themselves, the answer is a resounding NO, but luckily, one could point to the work of Oromia Support Group and The Human Rights League of the Horn of Africa for their specialty in putting specific ethno-national face to oft  effaced  torture in Oromia, Ethiopia.

Categories: Human Rights  Tags:

ዶ/ር መረራ የፍንዳታውን ዜና “እንጠራጠረዋለን” አሉ

"በአዲስ አበባው ፍንዳታ የሞቱት ኢትዮጵያዊያን ናቸው"
bole 1
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሩዋንዳ ሰፈር የደረሰውን ፍንዳታ አስመልክቶ ኢህአዴግ ያሰራጨውን ዜና የሚቃረኑ መረጃዎችና አስተያየቶች ቀረቡ። ለኢህአዴግ ቅርበት ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች የድጋፍ አስተያየት ሲሰጡ ዶ/ር መረራ “አትፍቶ ጠፊ አጥፍቶ ይጠፋል እንጂ በሜዳ ዝም ብሎ አያጠፋም” ሲሉ ጥርጣሬ እንዳላቸው ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ትህዴን/ በፍንዳታው የሞቱት ኢትዮጵያውያን ናቸው ሲል ስም ገልጾ የኢህአዴግን ዜና አጠጥሎታል።

የጌት አስ ኢንተርናሽናል ባለቤት እና ዋነኛው የወያኔ ባለድርሻ የንግድ አጋር ባሌለበት ተከሰሰ::

Photo: የጌት አስ ኢንተርናሽናል ባለቤት እና ዋነኛው የወያኔ ባለድርሻ የንግድ አጋር ባሌለበት ተከሰሰ::

ከረዥም ጊዜ ጥረት እና ድካም በኋላ በሕወሓት ባለስልጣናት ተከላካይነት ሲኖር የነበረው ዋነኛ ሙሰኛው አቶ ጌቱ ገለቴ የጌትኣስ አለማቀፍ ድርጅት ባለንብረት እንዲሸሽ ተደረገ:: ግለሰቡ ከተለያዩ የሕወሓት ባለስልጣናት እና ድርጅቶች ጋር ከፍተኛ የሆነ ሙስና የፈጸመ ሲሆን የሙስና ኮሚሽን ያቀረበበትን ክስ ተከትሎ ወደ ውጭ አገር እንዲሸሽ ያደረጉት መሆኑ ሲታወቅ የጸረ ሙስና ኮሚሽን ባቀረበው የፍርድ ቤት አቤቱታ ግለሰቡ ለመያዝ የክስ ዋረንት እንዲቆረጥለት የጠየቀ ሲሆን ከወር በፊት ከሃገር እንዲወጣ ያደረጉት የሕወሓት ባለስልጣናት ክሱን ለማድበስበስ ቢሞክሩም አልተሳካላቸውም::ለቤተሰቦቻቸው ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንዳሉት አቶ ጌቱ አሜሪካን አገር ይገኛል::

ከጉምሩክ ባለስልጣናት እና ከታሰሩ ነጋዴዎች ጋር በጥምረት ክስ የቀረበበት አቶ ጌቱ በቦሌ መስመር አፍሪካ መንገድ ሁለት ህንጻዎች ያሏቸው ሲሆን ከአቶ ከተማ ከአቶ ነጋ እና በቅርቡ ከተያዙት አቶ ገብረስላሴ የኮሜት ባለቤት ጋር የንግድ ቡድን ያላቸው መሆኑ ታውቋል:: 
READ MORE HERE http://ethiopianewsforum.com/viewtopic.php?f=2&t=63737
ከረዥም ጊዜ ጥረት እና ድካም በኋላ በሕወሓት ባለስልጣናት ተከላካይነት ሲኖር የነበረው ዋነኛ ሙሰኛው አቶ ጌቱ ገለቴ የጌትኣስ አለማቀፍ ድርጅት ባለንብረት እንዲሸሽ ተደረገ:: ግለሰቡ ከተለያዩ የሕወሓት ባለስልጣናት እና ድርጅቶች ጋር ከፍተኛ የሆነ ሙስና የፈጸመ ሲሆን የሙስና ኮሚሽን ያቀረበበትን ክስ ተከትሎ ወደ ውጭ አገር እንዲሸሽ ያደረጉት መሆኑ ሲታወቅ የጸረ ሙስና ኮሚሽን ባቀረበው የፍርድ ቤት አቤቱታ ግለሰቡ ለመያዝ የክስ ዋረንት እንዲቆረጥለት የጠየቀ ሲሆን ከወር በፊት ከሃገር እንዲወጣ ያደረጉት የሕወሓት ባለስልጣናት ክሱን ለማድበስበስ ቢሞክሩም አልተሳካላቸውም::ለቤተሰቦቻቸው ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንዳሉት አቶ ጌቱ አሜሪካን አገር ይገኛል::
ከጉምሩክ ባለስልጣናት እና ከታሰሩ ነጋዴዎች ጋር በጥምረት ክስ የቀረበበት አቶ ጌቱ በቦሌ መስመር አፍሪካ መንገድ ሁለት ህንጻዎች ያሏቸው ሲሆን ከአቶ ከተማ ከአቶ ነጋ እና በቅርቡ ከተያዙት አቶ ገብረስላሴ የኮሜት ባለቤት ጋር የንግድ ቡድን ያላቸው መሆኑ ታውቋል::
READ MORE HERE http://ethiopianewsforum.com/viewtopic.php?f=2&t=63737
#
Minilik Salsawi #

አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ኢትዮጵያ የሰቆቃ ደሴት ናት አለ

“ሂዩማን ራይት ዋች” በሚል የአንግሊዝኛ ምህጻረ ቃል የሚጠራዉ አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አዲስ አበባ ዉስጥ የሚገኘዉ ማዕከላዊ እስር ቤት ሰላማዊ ዜጎች (ጋዜጠኞች፤ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤ ወጣቶችና ባጠቃላይ ስርአቱን የሚቃወሙ ዜጎች) ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችል ሰቆቃ የሚፈጸምበት ቦታ ነዉ በማለት የወያኔ አገዛዝ በሰዉ ልጆች መብት ላይ የሚፈጽመዉን በደል ለአለም ህዝብ እንደገና ይፋ አደረገ። “እነሱ የሚፈልጉት ያሰሩት ሰዉ ሲናዘዝ ማየት ብቻ ነዉ” የአዲስ አበባዉ ማዕከላዊ እስር ቤት የሰቆቃና ሰላማዊ ዜጎችን የማሰቃያ ቦታ ነዉ በሚል መሪ ቃል በ70 ገጾች ታትሞ በወጣዉ የድርጅቱ ሪፖርት ላይ ከ35 በላይ ማዕከላዊ እስር ቤት ታስረዉ የወያኔን ግፍና መከራ በአይናቸዉ ያዩና ሰቆቃ የተፈፀማባቸዉ የቀድሞ እስረኞች የምስክርነት ቃል ተካትቶበታል።
 

የሂዩማን ራይት ዋች የአፍሪካ ዘርፍ ተጠባባቂ ዳይረክተር የሆኑት ወይዘሮ ሌዝሊ ሌፍኮ የኢትዮጵያ ባለስልጣኖች ሰላማዊ ዜጎችን አስረዉ ለማናዘዝ የሚያደርጉት ድብደባና የሚፈጽሙት ሰቆቃ እንኳን በጋዜጠኞችና በተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ላይ በጦር ወንጀለኞች ላይም ሊፈጸም የማይገባ ወንጀል ነዉና አለም ይሀንን አይነት በደል ህገ መንግስታዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ ሀሳባቸዉን በገለጹ ዜጎች ላይ ሲደርስ ዝም ብሎ መመልከት የለበትም ብለዋል። ማዕከላዊ እስር ቤት ዉስጥ የሚደረገዉ ምርመራ እስረኞችን የሚደበድብ፤ እስረኞች ዉስጥ እግራቸዉን ከተገረፉ በኋላ ለብዙ ሰዐታት በእግራቸዉ እንዲቆሙ የሚያደርግና አጥንት የሚሰነጥቅና የዘረኝነት ይዘት ያላቸዉ የቃላት ዉርጅብኝም እንደሚያጠቃልል ወይዘሮዋ የተናገሩ ሲሆን አንድ ከኦሮሚያ ክልል ተወስዶ የታሰረ ተማሪ እንደተናገረዉ ምግቡን ሲበላ ጭምር እግሩን እንደሚታሰርና እጅና እገሩን ታስሮ ለቀናት በጨለማ ቤት ዉስጥ እንደተጣለ ተናግሯል።

Monday, October 21, 2013

የኢህአዴግ ቀጣይ የፖለቲካ ሴራዎች – (ተመስገ ደሳለኝ)

October 21/10/20

ከ ተመስገ ደሳለኝ 

አዲስ አበባ

የሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ-ምህረት የመጀመሪያ ወር ተጠናቅቋል፤ አዳዲስ ክስተቶችም ታይተዋል፤ ያለፉት አስራ ሁለት ዓመታትንበጃንሆይ ቤተ-መንግስት ያሳለፉት ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፣ በኦህዴዱ ሙላቱ ተሾመ መተካታቸው አንዱ ነው፡፡ አባይ ፀሀዬና ዶ/ር ካሱ ኢላላም ከበረከት ስምዖንና ኩማ ደመቅሳ በተጨማሪ በሚኒስትር ማዕረግ የኃ/ማሪያም ደሳለኝ ‹‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር›› አማካሪ ሆነው መሾማቸው ሌላው ነው (በነገራችን ላይ ሹመቱን እንደተለመደው አይቶ ችላ ብሎ ለማለፍ የማያስችሉ ሶስት ምክንያቶች አሉ፤ የመጀመሪያው በሀገሪቱ ለአንድ የሥራ መደብ አራት ሚንስትር ተሹሞ አለማወቁ ሲሆን፤ ሌላው ተሿሚዎቹ፣ ኢህአዴግን ከመሰረቱት አራት ፓርቲዎች በኮታ የተወጣጡ መሆናቸው ነው፡፡ ሳልሳዊውና አስገራሚው ደግሞ ሰዎቹ ፖለቲከኞች እንጂ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ጥናትና ምርምር ያካሄዱ ምሁራን አለመሆናቸው ነው)
እነዚህ ሁሉ በግልፅ የሚታወቁ የዓመቱ መጀመሪያ ክስተቶች ናቸው፡፡ ለስርዓቱ ቅርበት ካላቸው ምንጮቼ ባገኘሁት መረጃ መሠረት፣ በቅርቡ ‹ሚዲያ›ን እና ‹የይቅርታ ስነስርዓት›ን የተመለከቱ አዳዲስ አዋጆች በተወካዮች ም/ቤት ለመፅደቅ ተዘጋጅተዋል፡፡ በተለይም ‹ሚዲያው›ን የሚመለከተው አዲሱ ህግ፣ ከአምስት ዓመት በፊት ተግባር ላይ የዋለውን የ‹‹ፕሬስ አዋጁ››ን የአፋና ጉልበት ይበልጥ የሚያጠናክር በመሆኑ፣ የነበረው አንፃራዊ ጭላንጭል ጭራሽ ሊዳፈን እንደሚችል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ‹‹የይቅርታ አዋጁ››ም ቢሆን ጥቂት የአገዛዙ ጉምቱ ባለስልጣናት ‹‹የተቃዋሚ ፓርቲ የአመራር አባላትና አንዳንድ የግል ጋዜጠኞች ብንታሰርም በይቅርታ እንፈታለን በሚል ግንባሩን እየተፈታተኑ ነው›› ሲሉ ደጋግመው መደመጣቸውን፣ ከአዲሱ ‹‹የይቅርታ አሰጣጥ እና አፈፃፀም ሥነ-ሥርአት አዋጅ›› ጋር ካያያዝነው፣ አንቀፆቹ ሊኖራቸው የሚችለውን አንድምታ መገመቱ ብዙ ከባድ አይሆንም፡፡

የጎሳ ፌደራሊዝም፤ ማንነት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካና የጎሳ ግጭት በኢትዮጵያ

የወያኔ መንግስት የተመሰረተበትና በዛሬይቱ ኢትዮጵያ የመንግስታዊ ስርዓት መሰረት የሆነው የጎሳ ፌደራሊዝም የጎሳን ማንነትና ልዩነትን ዓይነተኛ የፖለቲካ ማደራጃ አድርጎአቸዋል። የጎሳ ፌዴራሊዝም ዲሞክራሲያዊ ሳይሆን

Augustprisnominerade!

Augustprisnominerade!

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ

ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሚዋጋች ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዎች ባለፈው ዓርብ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ በተለይም አዲስ ኣበባ በሚገኘው እና ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ማዕከል በእስረኞች ላይ ይፈጸማሉ ባላቸው ሰብዓዊ ሰቆቃዎች ላይ ያነጣጠረ አዲስ ሪፓርት ይፋ ኣድርገዋል።

Zu: Boss von mexikanischem Golf-Kartell festgenommen - Neuer Schlag gegen Drogenmafia
A relative of an inmate observes policemen behind the security fence after a riot inside Apodaca prison, on February 20, 2012, near Monterrey, state of Nuevo Leon, Mexico. At least 44 inmates have been killed during a riot Sunday and about 30 alleged members of the drug cartel Los Zetas were rushed out from the prison. AFP PHOTO/Julio Cesar Aguilar (Photo credit should read Julio Cesar Aguilar/AFP/Getty Images)
ሰብዓዊ መብት ሲባል በነገስታት መልካም ፈቃድ የሚቸሩ ወይንም መንግስታት ከሚመሩባቸው ህግጋተ መንግስታት የሚመነጩ ብቻ ሳይሆኑ በ ተ መ ድ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌዎች መሰረት ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ በተፈጥሮ የተቀዳጁኣቸው መሰረታዊ የሰው ልጅ መብቶች ናቸው። በእነዚህ ህጎች መሰረት ደግሞ እንደ መኖ ኣልባሳት እና መጠለያ የመሳሰሉ የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ጨምሮ ዜጎች እንደ ህክምና እና ትምህርት የመሳሰሉ ማህበራዊ ፍላጎቶችን ሁሉ የማግኘት መብት ኣላቸው።
እናም ጥቂት ለማይባሉ ዓመታት እንዲያውም ዓስርተ ዓመታት ማለት ይቻላል በረኃብ አለንጋ ከሚገረፈው የኢትዮጵያ ህዝብ አንጻር ለምን የሚል ጥያቄ ቢቀርብላቸው እንደ ምክኒያት አዲሶቹ መንግስታት በቀድሞዎቹ ላይ እያላከኩም ቢሆን መልሳቸው ግን ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል። ድህነት። በእርግጥ የፖሊሲ ችግሮች ሳይዘነጉ ከድህነት ወለል በታች በምትገኘው ኢትዮጵያ ኣምኖ ለመቀበል ማስቸገሩ ባይቀርም ኣይደለም ብሎ ለመከራከር ግን ሊከብድ ይችላል።

“ለዋልያዉ ልጫወት”…በቻምፕዮንስ ሊግ የተጫወተዉ ዋሊድ አታ የስዊድኑ ሂልስነቦርግ ተከላካይ

ይህ ከዋሊድ አታ የስዊድኑ ሂልስነቦርግ ተከላካይ ለTeam Ethiopia የfacebook pageየተላከ ደብዳቤ ነዉ፤ተጫዋቹ በዩሮፓ ሊግ እና ቻምፕዮንስ ሊግ ተጫዉትዋል፤ለዋልያዉም ለመጫወት ፍላጎቱን የገለፀዉ ከናይጄሪያ ጨዋታ በፊት ቢሆንም ከዋልያ በኩል ምንም ምላሽ አላገኘም..ከዚህ ደብዳቤ ጋር አብሮ የተጫዋቹን እንቅስቃሴ የሚያሳይ ምስል አለ..እናም እናንት የዋሊድን ጥያቄና ምስሉን አይታችሁ ትፈርዱ ዘንድ እነሆ!!!
My name is Walid Atta, born in Riyadh in Saudi Arabia in August 28th 1986. My career as a professional football player started in early 2008 when I joined team AIK in Stockholm Sweden. Team AIK was founded in 1891 (122 years ago) and is measured as top club in the Swedish league for decades. During my engagement with AIK (3 years) I gained a lot of experience in all aspect of professionalism as a football player. Throughout these years a became a key player and performed very well in many games in the league also in some international games as well. These 3 successful years became my key to the Swedish national team of U21 and many offer from international clubs, like Glasgow Rangers from Scotland, Valencienne from France and Dinamo Zagreb from Croatia and a few more. After consulting family and my agent I decided to sign up for Dinamo Zagreb from Croatia. Less successful journey with injuries and unstable club economy leading to the club not been able to pay players’ salaries.  Subsequently free ticket from Dinamo Zagreb to leave the club and sin up for any other club with no obligation what so ever. Helsingborg IF, Swedish football clublocated in a city of  Helsingborg. the club was previous year champions of Swedish league which means Europa Champions League qualifications games to be played if I signed up for the club which I did. Successful story again many international games like hanover 96, Levante and Twente , 7 goals as a center back more than any defender in the league, many offers from clubs in Europe, and voted to be player of the year.

I  have been following the Ethiopian national team in African cup and world cup qualification and I am so impressed and proud how they are progressing just getting better and better It looks good and promising for Ethiopian football in future and hopefully I can be a part of that team and contribute to an even greater success, that would be a fantastic honor. Kind Regards
Walid Atta
http://www.youtube.com/watch?v=0xHxGnHlJ6M&feature=youtu.be

በጀርመን መዲና በርሊን እንብርት ላይ በሚገኘው በብራንድን ቡርገር ቶር አደባባይ ላይ፤ አፍሪቃን ጨምሮ ከሌሎች አህጉራት የተሰባሰቡ ስደተኞች ለአስር ቀናት

አፍሪቃዉያን ስደተኞች የረሃብ አድማ በጀርመንTitel: Flüchtlinge am Brandenburger TorSchlagworte:Flüchtlinge, Brandenburger Tor, Hungerstreik, Berlin, LampedusaWer hat das Bild gemacht?: DW/Lavinia PituWann wurde das Bild gemacht?: 14.10.2013Wo wurde das Bild aufgenommen?: Berlin, Pariser PlatzBildbeschreibung: Flüchtlinge befinden sich seit mehreren Tagen im Hungerstreik, am Pariser Platz. Sie verlangen Asyl in Deutschland und Änderungen der deutschen Einwanderungspolitik.
በርሊን ከተማ በታዋቂዉ የብራንድን ቡርገር ቶር አደባባይ ላይ አድማ ሲያደርጉ ከቆዩት 30 ከሚሆኑ ስደተኞች መካከል ኢትዮጵያዉያንም ይገኙበታል። የበርሊኑ ወከላችን ይልማ ሃይለሚካኤልን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት ስለ ረሃብ አድመኞቹ ስደተኞች ጉዳይ ጠይቄዉ ነበር
አዜብ ታደሰ
ይልማ ሃይለሚካኤል
ለመስማት የሚቀጥለውን ይጫኑ

“ኢትዮጵያነቴን ይዤው ወደ መቃብር እሄዳለሁ” አቶ ተስፋዬ ገ/አብ

ቀደም ብዬም ተናግሬያለሁ። ማንም ሊከለክለኝ አይችልም። ማንም ሊሰጠኝ አይችልም። አገር ውስጥ እንዳልገባ ልከለከል እችል ይሆናል። የልብ ስሜቴን መንጠቅ የሚችል አንድም ሰው የለም። ይህንን ስሜቴን ነው ባጭሩ ማነገር የምፈልገው።ማንም አይቻለውም። ኢትዮጵያዊያን ወንድሞቼ ሚሊዮኖች አሉ።በተለያዩ ምክንያቶች አገር ቤት መግባት አይችሉም። ከጥቂት ጊዜያት  በሁዋላ ግን እንደጎርፍ ነው ወደ አገራችን የምንገባው።ይህንን ነው ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው። / አበባ ይበተንለታል/ ለከለከሉኝ ክፍሎች ማን ነው ያ ከልካይ በመሰረቱ? ከየት ነው የመጣው? ያ ሰው ምን አደረገ ለአገሪቱ?እኔ የቢሾፍቱ ልጅ ነኝ። ኢትዮጵያዊ ነኝ። ይህንን መከልከል የሚችል ማንም የለም።ይዤው ወደ መቃብር እሄዳለሁ። እስከመጨረሻው … (ተስፋዬ ከኢካድኤፍ የመወያያ መድረክ ጋር ካደረገው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ)
 
 
ከሰነዱ ከተገኙት መረጃዎች መካከል ተስፋዬ በእጁ የጻፈው ይህ መረጃ ይገኛል፡-
“ኢትዮጵያዊያን የኤርትራ ታሪክ በትክክል እንዲያውቁ ይረዳል። ይህም በአዲሱ የኢትዮጵያ ትውልድ አእምሮ ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል እንዳልነበረችና እንደማትሆንም የአመለካከት ዘር መዝራት ያስችለኛል። ለዚህ ሥራም የናንተ መ/ቤት ሆነ ህገደፍ (ሻዕቢያ) ሰነዶችን እንድመለከት በመፍቀድ ያግዘኝ ዘንድ እመኛለሁ። እነዚህ መጻሕፍትን ጽፌ እስከምጨርስ ሁለት ዓመት ይፈጅብኛል። ቢያንስ በቢሮና በጽሕፈት መሣሪያዎች እንዳልቸገር ብደረግ እመኛለሁ።” …

“በኤርትራ ጉዳይ፣ በሻዕቢያ አላማዎችና አሰራሮች፣ እንዲሁም ኢሳያስን በተመለከተ ያለኝ በጣም ግልጽ ነው። ከነሙሉ ችግራችን ኤርትራ በትክክለኛው ሃዲድ ላይ እየተጓዘች ነው ብዬ አምናለሁ። የሚታረሙ ነገሮች ካሉ ዋናው ጉዞአችን ሳይነካ እየተስተካከለ ሊሄድ ይችላል ብዬ አምናለሁ። የምጽፈውም ሆነ የምሠራው ይህን መሠረት ያደረገ ነው።” …


“አሻግሬ ስመለከት በርቀት ሰማያዊ ተራሮች ይታየኛል። ከተራሮቹ ስር ያለው ለጥ ያለ የእርሻ ሜዳ የአባቴ አገር ነው።” …
“ይህን ታሪክ እጽፈዋለሁ: 3 ተከታታይ መጽሐፍ ሊወጣው ይችላል። ባህረነጋስያን በመጀመር የኤርትራን ታሪክ እጽፈዋለሁ። የሻቢያን የትግል ታሪክ እጽፈዋለሁ። ይህም ኢትዮጵያዊያን ስለኤርትራ ተገቢውን ሃቅ እንዲገነዘቡ ያደርጋቸዋል። በዚህ መጽሐፍ ጠላት አፈራለሁ። ቢሆንም ግን እጽፈዋለሁ። ስለዚህ ከአሁኑ ፍንጭ መስጠቱ ጠቃሚ ነው። በተቃውሞ የምጽፍ የሚመስላቸው ስለሚኖሩ እስከዚያው ድረስ ይዝናኑበት። ኤርትራ ለመመለሴ ምክንያት ይሰጥልኛል።”
golgule.com

Monday, October 21, 2013

የብኣዴኑ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከግድያ አመለጠ::


የብኣዴኑ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከግድያ አመለጠ:: #Ethiopia #Ogaden #eprdf #ONLF የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ሰራዊት በቀብሪደሃር አየር መንገድ (AIRPORT) የወያኔ ባለስልጣናትን አጠቁ:: ብዛት ያላቸው የወያኔ ወታደሮች ሲገደሉ 2 መኪናዎች ተቃጥለዋል:: በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራው የወያኔ ባለስልታናት የሃገር ውስጥ ባለሃብቶች እና ወታደራዊ መኮንኖች የያዘ የልኡካን ቡድን በኦጋዴን ክልል እንደደረሰ በኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ሰራዊት በተከፈተበት ቶክስ በርካታ ወታደሮች ሲገደሉ ባለስልጣናቱ ማምለጣቸው ታውቋል:: ዋናው አላማችን ወደ ባለስልጣናቱ ማነጣጠር አልነበረም ሆኖም የህንን የወያኔ ባለስልጣናት ጉብኝት ማደናቀፍ እና ለአሻንጉሊቱ አስተዳደር መልእክት ማስተላለፍ ነበር ሆኖም በተገኘው አጋጣሚ አየር መንገዱን አጥቅተን የወያኔ ወታደሮችን ፈጅተናቸዋል::ወታደሮቹ ለእንግዶቹ ጥቃት እየተፈጸመ ስለሆነ መረጃ በመስጠት እንዲያመልጡ ቢያደርጓቸውም ባለስልጣናቱ አብረዋቸው ላሉት የህንን ጉዳይ ለማድበስበስ ሞክረው ነበር::ሆኖም አላማችን ተሳክቷል ወያኔንም አስደንግጠናል ብለዋል የግንባሩ ቃል አቀባይ:: @[152231248121039:274:EthiopianReview]  # Minilik Salsawi#

የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በውጥረት ላይ ነው – አካባቢው በፌደራል ፖሊስ ተወረረ

በደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና በመንግስት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እየተካረረ መሄዱ ታወቀ። የሃይማኖት ልብስ ለብሳችሁ ወደ ዩኒቨርሲቲው መግባት አትችሉም በሚል መንግስት በክርስቲያን እና በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ባወጣው አዲስ መመሪያ የተነሳ ተናሪዎቹ የምግብ ጥራትን እና ሌሎች ጉዳዮችን አክለው በትምህርት ቤቱ ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ እንደነበረ ዘ-ሐበሻ ከቀናት በፊት መዘገቧ ይታወሳል። ዛሬ ከደብረ ማርቆስ በፎቶ ግራፍ ተደግፎ በደረሰን መረጃ መሰረት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የትምህርት ቤቱ አካባቢም በፌደራል ፖሊሶች ተወሯል። ፎቶቹ የሚከተሉት ናቸው። ዝርዝሩን ተከታትለን እንዘግባለን።
polci
(ዘ-ሐበሻ)

Systematisk tortur av politiske fanger i Etiopia


October 20/2013

Etiopisk opprørspoliti slo hardt ned på opptøyene i landet i 2005. Siden den gang av menneskerettighetssituasjonen i landet forverret seg kraftig, ifølge Human Rights Watch.
FOTO: ANDREW HEAVENS, REUTERS

Systematisk tortur av politiske fanger i Etiopia

Opposisjonspolitikere, journalister og regimekritikere blir utsatt for systematisk tortur på en politistasjon i Addis Abeba, viser ny rapport
Torturmetodene som brukes er blant annet slag mot kroppen med harde gjenstander og pisking. Fanger blir også hengt fra taket i svært smertefulle posisjoner.

“በ15 ቀን ውስጥ ከወልቃይት ጠገዴ ሁለት ሺ ተማሪዎች ተፈናቅለዋል”መአህድ

የመላው አማራ ህዝብ (መዐህድ) በአማራ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው መፈናቀል በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ፡፡ መአህድ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ የአማራ ተወላጆችን መፈናቀል በተመለከተ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ማሳወቁንና መፈናቀሉ እንዲቆም መጠየቁን ጠቁሞ፤ ጉዳዩ እስካሁን እልባት አለማግኘቱን ገልጿል፡፡

የህውሃት ኢሃደግ መንግስት በልጆቼ ለምን ዘመተ? (ከኣስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል) ሁለተኛ ልጄ ክብሮም እንደ ወንድሞቹ የእስር ሰለባ ሆነ፡፡እኔ ለኢትዮፕያ ህዝብ ጠላት ሳልሆን ፍፁም ወዳጁ ነኝ መጀመርያ ደርግን 17 ኣመት በመታገል ፋሽሽታዊ ደርግ በማስውግድ ኣስተዋፅኦ ነበረኝ፡፡ ህውሃት ኢህኣደግ ስልጣን ከያዘ በሃላም ለንሮየ ለደሞወዝ ሳላስብ 17 ኣመት ሙሉ የታገልኩበት ኣላማ ስለተቀለበሰ በተጨማሪ የህውሓት መሪዎች ለኢቲዮፕያ ሉኣላዊነትና ኣንድነት ታማኝነት ስላጎደሉ የኢትዮፕያ ሕገመንግስት በሚፈቅደው መሰረት በግልም በፓርቲ ተደራጅቼ እየታገልኩ ቆይቼ ኣሁንም እታገላለው ታድያ እኔ በሃገራችን ሕ/መንግስት በሚፈቅድልኝ መሰረት መታገሌ እንደ ሃጠያት ተቆጥሮ የቂም በቀል ፖለቲካ ወደ ልጆቼ ምን ኣመጣው ይህ ለማለት የፈለጉኩት፡፡

ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ለሥራ መሄድ ሊታገድ ነው


ሳዑዲ ዓረቢያ በየወሩ እስከ 10 ሺሕ የቤት ሠራተኞችን ከኢትዮጵያ ትፈልጋለች
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ባለፈው ሐሙስ በተወካዮች ምክር ቤት አባላት አዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ያደረጉትን ንግግር በማስመልከት ጥያቄ

ቀርቦላቸው ባስረዱበት ወቅት፣ ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ለሥራ የሚሄዱ ሰዎች ከመጪው ወር ጀምሮ ከመሄድ እንደሚታገዱ አስታውቀዋል፡፡

Sunday, October 20, 2013

በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ክፍለ ከተማ በፈነዳው ፈንጅ የሞቱት ዜጎች ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ተረጋገጠ፣





ጥቅምት 3/2006 ዓ/ም በአ/አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ በፈነዳው ፈንጅ የሞቱት ዜጎች ሶማሊያዊያን መሆናቸውን የሚገልጽ በኢህአዴግ ሚድያ የተሰራጨው ዘገባ ለፖለቲካ ፍጆታ ተብሎ የተደረገ እንደሆነና በአደጋው የሞቱት ሁለት ሰዎች ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን በመታወቅያ ወረቀታቸው ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን የሟቸቹ ስምም ምክትል ኢንስፔክተር ሞላ መላኩ የተባለ የፖሊስ አባልና አቶ ሞገስ አስቻለው የተባለ ሲቪል መሆናቸውን ከአከባቢው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል፣
ከአደጋው ጋር በተያያዘ በአከባቢው ታይታችሃል በሚል በርካታ የተቃዋሚ ድርጅት አባላት የታሰሩ ሲሆን ከነዚህም መካከል አቶ ፍስሃ ገ/ዮዋሃንስ ፤ አቶ አብርሃ ታወቀና አቶ መርእድ ገ/ስላሴ የተባሉ የኢዴፓ አባላት ይገኙበታል፣

በኦጋዴን የነዳጅ ጉድጉድ ቁፋሮ ተጀመረ

በኦጋዴን የነዳጅ ጉድጉድ ቁፋሮ ተጀመረ

ኒው ኤጅ የተሰኘው የእንግሊዝ ኩባንያ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኦጋዴን ቤዚን፣ ኤልኩራን በተባለ ሥፍራ የነዳጅ ጉድጓድ ቁፋሮ ጀመረ፡፡ ኒው ኤጅ በኦጋዴን ብሎክ ሰባት፣ ስምንትና አዲጋላ በተባለ ድሬዳዋ አቅራቢያ በሚገኙ የነዳጅ ፍለጋ ቦታዎች አፍሪካ ኦይል ከተሰኘ የካናዳ ኩባንያ ጋር በነዳጅ ፍለጋ ሥራ የተሰማራ ኩባንያ ነው፡፡ ኩባንያው ኤልኩራን በተባለ በሶማሊያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ አካባቢ የነዳጅ ጉድጓድ ቁፋሮ ጀምሯል፡፡ታማኝ የዜና ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኩባንያው የመቆፈሪያ ማሽኑን ተክሎ የቁፋሮ ሥራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ሳለ የቁፋሮ ባለሙያዎች በማሽኑ ላይ የቴክኒክ ችግር በማግኘታቸው የቁፋሮ ሥራውን ሳይጀምሩ አዘግይተውታል፡፡ ባለሙያዎቹ በማሽኑ ላይ ያገኙትን የቴክኒክ ችግር አስወግደው የቁፋሮ ሥራውን ባለፈው ሳምንት መጀመራቸውን ምንጮች ተናግረዋል፡፡


የሚቆፈረው ጉድጓዱ ጥልቀት 2,800 ሜትር እንደሆነና የቁፋሮውን ሥራ ለማጠናቀቅ ሦስት ወራት ያህል እንደሚፈጅ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከሦስት ወራት በኋላ በጉድጓዱ ውስጥ ነዳጅ መኖርና አለመኖሩን የሚጠቁም የሙከራ ሥራ እንደሚሠራ ታውቋል፡፡
አፍሪካ ኦይል በቅርቡ በድረ ገጹ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ከኒው ኤጅ ጋር በመተባበር በኦጋዴን ላይ አተኩሮ እንደሚሠራ ገልጿል፡፡ አፍሪካ ኦይል በኤልኩራን የነዳጅ ክምችት እ.ኤ.አ. በ1970ዎቹ መገኘቱን ጠቅሶ፣ አሁን በሚቆፈረው ጉድጓድ በአካባቢው የሚገኘውን የነዳጅ ክምችት መጠን ለማወቅ እንደሚቻል አስታውቋል፡፡


‹‹በኤልኩራን ነዳጅ መኖሩ ይታወቃል፡፡ አሁን ዋናው ሥራ የሚሆነው በሚቆፈረው ጉድጉድ ውስጥ የነዳጅ ፍሰት እንዲከሰት በማድረግ በአካባቢው የሚገኘውን የነዳጅ ክምችት መጠን ማወቅ ነው፤›› ብለዋል ምንጮች፡፡

ሪፖርተር ያነጋገራቸው የፔትሮሊየም ባለሙያዎች በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ቴኔኮ የተባለ የአሜሪካ ኩባንያ በኤልኩራን በቆፈረው የመጀመሪያ የነዳጅ ፍለጋ ጉድጓድ የተፈጥሮ ዘይት ፍሰት ማግኘቱን አስታውሰው፣ በወቅቱ ኩባንያው ክምችቱ በቂ አይደለም በሚል ትቶት ሄዷል ብለዋል፡፡ አክለውም አሁን ባለው ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቅመው አፍሪካ ኦይልና ኒው ኤጅ በኤልኩራን ከፍተኛ መጠን ያለው የነዳጅ ክምችት ሊያገኙ እንደሚችሉ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡ ዜናው የሪፖርትር ነው።
ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ

Eritrean Norwegian 23 Left a Wife and a Newborn to Fight a Jihad War in Syria

Islamic Jihad militants take part in the funeral of their comrade Mahmoud Shaath in Khan Younis, in the southern Gaza Strip Eritrean Norwegian 23 Left a Wife and a Newborn to Fight a Jihad War in Syria
How did 23-year-old’s life from pike fishing to holy war
As a youth he loved pike fishing. Now he is fighting in Syria.
By kadafi Zaman | http://www.tv2.no
According to the Police Security Service (PST) has at least 30 to 40 people traveled from Norway to fight in Syria. Now, TV2 tell the story of one of them, 23-year-old “Ali”. He came from Eritrea to Norway as an unaccompanied migrant on September 9th 2003. When he was only 13 years.
The first residence was a reception center just outside Oslo. After a short time he had a Norwegian foster family in Bærum. Tor Bach in the multicultural outdoor organization Wild X was often visited by Norwegian-Eritreans.
- I remember him as a happy, well-adjusted and securely boy who got along with everyone, says Bach.2223-year-old “Ali” came to Norway as an unaccompanied asylum He says that the boy was with several fishing trips arranged by leisure organization. - We were ice fishing and pike fishing. He got one six-pound pike. He was brilliant bland and very proud to have received the pike is, says Bach.
- Talked about shooting Jews
For five years the boy lived with his Norwegian foster family. He played football and got good grades from high school.
TV 2 has spoken to several sources familiar with Norwegian-Eritreans. They will not stand up, but describes him as a dutiful and kind person.
In 2010 he worked as a nursing staff member at an institution in Bærum. He worked for a time as well as a student assistant at a school in Drammen.
Right after high school he moved to Volda to study.
According to TV2′s sources, he changed himself after he left home. They say that he came back shortly with a more conservative approach to the religion of Islam.
Spring 2012 called Norwegian-Eritreans to Tor Bach and asked if he could take hunting test with three friends. Bach welcomed him, but said he was surprised when they met.33 seeker in 2003. © Private According to TV2′s sources changed the 23-year-old “Ali” after he left home. © Private
- I saw a completely different boy. Then I saw a guy with a long beard and angry eyes, and friends who talked about shooting Jews, says Bach. Do you have tips about this matter? Contact us attips@tv2.no
Radicalized in a short time
TV 2 is known that the three individuals Norwegian-Eritreans had with them are key figures in the extreme grouping Prophet’s Ummah.
- They would have access to weapons and thought that hunting proficiency test course was a great way to arrange it. We managed to sabotage so that none of them had access to weapons, says Tor Bach.
From January 2011 to September 2012 worked the then 22 year old man as a parking guard in Oslo. During this period he also married a Norwegian-Eritrean woman.
According to TV2′s sources were Norwegian-Eritreans radicalized within a very short time. He was greatly inspired by jihadist propaganda films from Syria.
In December 2012 left the 23-year-old Norway and headed for Syria. Back set one wife and one just a few weeks old baby.
Deleted Facebook account For the first time tells the Police Security Service about how many people have traveled from Norway to fight in Syria. - We assume that there may be between 30 and 40 people, but it is unrecorded and figures may be higher, says the PST-head Benedicte Bjørnland to TV 2
For ten months, the 23-year-old fought in Syria. TV2 know that he is alive and that he is in jihadistbrigaden, Kataib al-Muhajereen. It is associated with the so-called al-Nusret-front.
- We are seeing a worrying increase in traveling from Norway to conflict areas. Previously we have not seen so many go at once so adapted to the same place, says Bjørnland.
- Where do they travel?
- It is primarily Syria, says PST boss.
Norwegian-Eritreans deleted a short time ago his Facebook account and there is almost no trace of him on the internet. It has not succeeded TV 2 to get in touch with the man.
Software Translation from Norwegian
http://eastafro.com/
ኡኦኡኡኡኡኦኡኡኡ
ብትጮሆስ ማን ሰምቶህ ማንስ ሊደርስልህ
አገር እንደሌለሽ ወገን እንደለለህ እሚያተርፈህ አተህ
ካገርህ ተሰደህ ያችን ሚስኪን ሃገር ነጸ አወጣብለህ
ያችን ሚስኪን እናት እርዳለሁ በልህ
የባእዳን ሃገር ባህሩ ሲበላህ
ኡኡኡኦኡ

ያንችን ወላጅ እናት አይኖዋን እንዲትልየው
ስማኳዋን ሳትጠግብህ ስደት የወጣህው
ስደት ሳይሆንልህ ባሀር የቀረህው
አላማህ ገብቶኛል ተረክቢሃለሁ
አደራህ አለበኝ እኔ አሳከዋለሁ
ላገርየ ነጰነት ለማምየ ጉልበት እኔሆናታለሁ
የወያኔን ሴራ እኔ አከሽፈዋለሁ
የአንድነት ፋና እመልሰዋለሁ !!!!!!
የአንድነት ፍና እመልሰዋለሁ
ድል ለሀገራችን
ሞት ለወያኔ
Lemlem Andargie

ከሙስና ጋር በተያያዘ ኢህአዴግ ችግር ውስጥ መሆኑን አቶ ሰብሃት ተናገሩ

ጥቅምት ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ከሙስና መንሰራፋት ጋር በተያያዘ የገጠመውን ፈተና በድል ለመወጣት ሕዝቡን ማሳተፍ እንዳለበትና ያለሕዝቡ ተሳትፎ የሚደረጉ ነገሮች ሁሉ የማይመለስ ጥፋትን ያስከትላሉ ሲሉ አቶ ስብሃት ነጋ ለኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮችን ምክር ለግሰዋል። የጸረ ሙስና ኮምሽን በሸራተን ሆቴል ያዘጋጀውና በምክትል ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር እና የፓርላማው አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ በመሩትና ዛሬ በተጠናቀቀው ስብሰባ ላይ የተገኙት የቀድሞ የህወሃት ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ስብሃት ነጋ ፣ በጸረ ሙስና ትግሉ ሕዝብ እንዲካፈል መጀመሪያ መታወቅ አለበት ካሉ በኃላ ” እኛ ህዝቡን አሳውቀነዋል ወይ?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አንድ መ/ቤት 200 ሰራተኞች ቢኖሩት እነዚህ ሰራተኞች በመ/ቤታቸው ጉዳይ የመጨረሻ አዋቂ መሆናቸውን በምሳሌነት የጠቀሱት አቶ ሰብሃት፣ ይህ አዋቂ ሕዝብ እንዳይታዘበን፣ የማይቀበለውን ቃል ተናግረን እንዳናጭበረብረው መጠንቀቅ አለብን ብለዋል፡፡ ኢህአዴግ ይህን አዋቂ ሕዝብ ካልያዘ የሚገጥመው ችግር ለመመለስም የማይቻል ነው ሲሉም አስጠንቅቀዋል፡፡ ሙስና በአሁኑ ወቅት የሌለበት አንድም መንደር የለም የሚሉት አቶ ስብሃት ፣ “ለመሆኑ የሙስናን መንስኤ ታውቁታላችሁ ወይ፣ መንስኤው ፓርቲው ነው፣ ነጋዴው ነው፣ የውጪ ኃይሎች ናቸው?’ ለመሆኑ መጠኑስ ስንት ነው፣ በመቶኛ ስሌት ስንት ነው፣ ስንት ሚሊየን ብር ጠፋ?” ሲሉ እነአቶ ሙክታርን በጥያቄ አፋጠዋል፡፡ መንስኤው ካልታወቀ ቀጣዩ ምንድነው ያሉት አቶ ስብሃት፣ በማታውቀው ነገር ልትታገል፣ ለውጥም ልታመጣ አትችልም በማለት የሙስና ሁኔታ በተጨባጭ ጥናት እንዲደገፍ ጠይቀዋል፡፡ የደረንስንበት የሙስና ሁኔታ ቀላል ስላልሆነ ይህን ጠርገን ንጹህ መሬት መቼ እናገኛለን ሲሉ ጥያቄ አዘል አስተያየታቸውን አክለዋል። አቶ ሙክታር ከድር የተነሱትን ሃሳቦች በገንቢነቱ እንቀበላለን ካሉ በኃላ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም በመባል የሚታወቀው ፕሮግራም የታሰበውን ያህል ለውጥ አለማምጣቱን በመጥቀስ ይህ ችግር ሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነትን ለመዋጋት አዳጋች ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ስብሰባ ስለሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነት አሳሳቢነት ትምህርት ሲሰጡ ከዋሉት ባለስልጣናት መካከል አቶ አባዱላ ገመዳ በአንድ ወቅት በሙስናና ብልሹ አሰራር በፓርቲያቸው ሰብሰባ ላይ ተገምግመው በትርፍነት የያዙትን መኖሪያ ቤት ለኦህዴድ እንደሚያስረክቡ ቃል በመግባታቸው በሕግ ሳይጠየቁ የታለፉ ሲሆን ቤቱን ግን በገቡት ቃል መሰረት ለፓርቲው አለማስረከባቸው ታውቆአል፡፡ እንዲህ ዓይነት በሙስና የተጨማለቁ ባለስልጣናት ስለሙስና አስተማሪና መድረክ መሪ ሆነው መታየታቸው ኢህአዴግ አሁንም ከባድ ችግር ውስጥ ስለመኖሩ ጠቋሚ ነው በማለት አንዳንዶች ለዘጋቢው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ግሎባል ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ የተባለው ተቋም በኢትዮጵያ እስከ 3 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በእየአመቱ ወደ ውጭ ተዘርፎ እንደሚወጣ ከአመት በፊት ባወጣው ሪፖርት መጥቀሱ ይታወቃል። አቶ ስብሀት ነጋ በአንድ ወቅት ይመሩት የነበረው ኢፈርት የተባለው ግዙፉ የህወሀት ኩባንያ እንዲሁም የህወሀት ባለስልጣኖች እና የመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች በአገሪቱ ውስጥ በተንሰራፋው ሙስና ዋነኞቹ ተዋናዮች መሆናቸው በተደጋጋሚ ይዘገባል።

የህወሓትን ፀረ ኢትዮጵያ አካሄድና ዓላማ በመቃወም የሕይወት መስዋእትነት የከፈሉ አመራር ነበሩ ወይ?

TPLF-Logo

ከነበሩስ እነማን ናቸው?
ከዚህ ቀጥለን የምንመለከተው ትኩረት ያልተሰጠውን ተሸፍኖ የነበረውን እና የህወሓት መሪዎች፣ በሕይወት ያሉትም የሞቱትም፣ ከወያኔ የተባረሩ አመራርም ጉዳዩ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ተዳፍኖ እንዲቀር ከባድ ጥረት እያደረጉበት ያለውን ነው።
በህወሓት የተፈጸመው እውንተኛ ታሪክና አሰቃቂ ወንጀሎች፣ የህወሓት አመራር በኢትዮጵያ ሃገራችን አሁንም  እየፈፀሙት የሚገኘው ግፍ በግልጽ ተጽፎ የወያኔ ጥቁር ታሪክ ለሕዝብ የሚቀርብበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። አሁንም እየቀረበ ነው።
ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) ለትግል የተሰማራው በየካቲት 11 ቀን 1967 ደደቢት በረሃ እንደመሸገ  ማሀብር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ (ማገብት) የተዘጋጀው ፕሮግራም የተረከበው ተሓህት ወይም የዛሬው ስሙ ሀወሓት ነው።
ተሓህት ትግሉን በጀመረበት ወቅት ጥቂት ከነበሩት ታጋዮች ሊመሩን ይችላሉ ብሎ ከመረጣቸው መካከል፤ 1. አረጋዊ በርሄ፣ ሊቀመንበር  2. ዘርኡ ገሰሰ 3. ግደይ ዘርአጽዮን 4. ገሰሰው አየለ 5. አባይ ፀሃየ 6. ሥዩም መስፍን 7. አለምሰገድ መንገሻ 8. አስፍሃ ሃጎስ ተመርጠው ተሓህትን መርተዋል።
በዚህ ጊዜ ነበር የማገብትን ውርስ ተሓህት ተረከበው ብሎ በጊዜው የነበረ ታጋይ ደስታውን የገለጸው። ውርስ ማለት ፕሮግራሙ ነው። በጊዜው የነበረ ሁሉም ታጋይ ግን የፕሮግራሙን ይዘትና ምንነትቱን አያውቅም ነበር።  ይህ ፕሮግራም ነበር በ1968 ቀስ በቀስም ተሓህትን ለሁለት የመሰንጠቅ አደጋ የፈጠረበት።
 የተሓህት-ህወሓት የመጀመሪያ መሰንጥቅ
ተሓህት ገና ከደደቢት በረሃ ሳይወጣ በፊት በሁለት ጎራ የተሰነጠቀበት ወቅት ነው። ይህን መከፋፈል የፈጠረው የፕሮግራሙ ባለቤት ነን የሚሉ አመራር በድብቅና ከታማኝ ታጋዮች ጋር በመተባበር ወስጥ ለውስጥ ፕሮግራሙ ይዘጋጅ ነበር። ይህን የማይደግፉና የሚቃወሙ አመራርም ነበሩ።
አክራሪና በአቋማቸው የጸኑ ግን ፕሮግራሙ በትክክል የተዘጋጀ ሃቀኛ የትግራይ ሕዝብ ምኞትና ፍላጎትን በጭብጥ ያስቀመጠ፤ ትግራይን እና ሕዝቧን ከአማራው ቅኝ አገዛዝ ነፃ የሚያወጣ፣ የትጋላችን መርህ ፕሮግራም ነው አሉ። የዚህ ተሳታፊውች፤ 1. አረጋዊ በርሄ 2፣ አባይ ፀሃየ 3. ሥዩም መስፍን 4. ግደይ ዘራጽዮን 5. ስብሃት ነጋ 6. መለስ ዜናዊ 7. አስፍሃ ሃጎስ 8. አውአሎም ወልዱ 9. ስየ አብርሃ 10. ሃይሉ መንገሻ ናቸው። እነዚህ ሁሉ አመራር የነበሩና ጥቂቶቹ ደግሞ ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ አመራር የመጡ ናቸው።
በሁለተኛ ደረጃ በተቃውሞ የቆሙትና ፕሮግራሙ በጣም አደገኛ፣ ኢትዮጵያን የሚያፈርስ፣ ሕዝብ በታኝ፣ ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነት ነው በማለት የተነሱት ደግሞ 1. ገሰሰው አየለ 2. አግአዚ ገሰሰ 3. አጽብሃ ዳኘው 4. ዶ/ር አታክልት ቀጸላ ሲሆኑ፣ ከሻእቢያ መጥቶ ተሓህትን የተቀላቀለው መሃሪ (ሙሴ) ተክሌም 5ኛ ሆኖ ከነገሰሰው አየለ ጋር ተቀላቀለ። እነዚህ ሁሉም የተሓህት አመራር የነበሩ ናቸው።
ማህበር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ (ማገብት) ገና ሲፈጠር ጎባጣ፣ ጸረ-ኢትዮጵያና ጸረ-ሕዝብ ሆኖ ነው የተመሰረተው። ይህንን ውርስ ያስረከበው ለተሓህት በየካቲት ወር 1967 ነው። በደደቢት በረሃ ተጠናክሮ ፕሮግራም ሆነ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ፕሮግራሙን በመቃወም የተሰለፉት ያነሱት ነጥብ፤
  1. ተሓህት በጸረ ኢትዮጵያና በሕዝቧ ተቀናጅቶ መፈጠሩ ኢትዮጵያ የምትባለውን ሃገር መበታተን አለባት የሚለው በገጽ 8 የተዘጋጀው የባእዳን ሴራና ጸረ ሃገር ነው፣
  2. አማራ የትግራይ ሕዝብ ጨቋኝና ረጋጭ፤ ለድህነት፣ ለሽርሙጥና፣ ለስደት፣ ለመከራ የዳረጋት ጠላት ነው የሚለው ትንተና ሃቅነት የሌለው የፈጠራ ወሬ ነው። የተጻፈው አማራን ሆን ብሎ ለማጥቃት ነው። ይህም ከፕሮግራሙ መወገድ አለበት፣
  3. ኤርትራ የአማራው (ኢትዮጵያ) ቅኝ ግዛት ናት የሚለው ቅንጣት ታህል ሃቅነት የሌለው እናንተ አመረር የፈጠራችሁት የተገንጣይ ዓላማ ነው፣
  4. ትግራይ የአማራ ቅኝ ግዛት ናት ማለት የአእምሮ ድህነትና ጠባብ ዘረኝነት ነው፣ ስለሆነም መወገዝ አለበት።
  5. ተሓህት የኢትዮጵያ ጥንታዊና ታሪካዊ ግዛትዋን እና የባሕር በሯን የሚያስነጥቅ ፕሮግራም ነው። ስለሆነም ጸረ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነት ነው። ፕሮግራሙ ይለወጥ ወዘተ. የሚሉ ሃሳቦች በማንቀሳቀስ ቀሪው ታጋይም የእነገሰሰው አየለን ሃሳብ መደገፉን በወቅቱ የነበሩ ታጋዮች በትክክል ተናግረውታል።
 በተጨማሪም አጽብሃ ዳኘው፣ ዶ/ር አታክልት ቀጸላ የጨመሩበት ነጥብ ተሓህት በትግራይ ሕዝብ ተቀባይነት ወይም የውክልና መሰረት የሌለው፣ ፕሮግራሙን በትግራይ ሕዝብ ስም መዘርጋት አግባብነት የሌለው፣ በሕዝብ ስም ማጭበርበር ነው ብለው በማመን በወቅቱ የነበሩ አነስተኛ ታጋዮች በዚህ ሃሳብ ተስማሙ። በዚህ ጊዜ 1. በስብሃት ነጋ 2. መለስ ዜናዊ            3. አውአሎም ወልዱ 4. ስየ አብርሃ ወዘተ. ተባብረው በአቶ ገሰሰው አየለ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ ጀመሩ። በስብሃት ነጋ እየተመሩ የገሰሰው አየለን ስምና ዝና በጥቁር ቀለም ቀቡት። ሻእቢያም ገሰሰው ከተሓህት ተቀላቅሎ መታገሉን ከመጀመሪያው ያልተቀበለው ስጋት ወስጥ ስለጣለው ነው። ሻእቢያ ለተሓህት አመራር ያስተላለፈው መልእክት፣ ገሰሰው አየለ በዚህ ከቀጠለ ተሓህትም ሆነ ሻእቢያ ትልቅ አደጋ ላይ እንደሚወድቁ ተናግሯል። ገሰሰው አየለ ከምድረ ገጽ መጥፋት አለበት የሚለውን የተህሓት ጥቂት አመራር ሃሳቡን ተቀበሉት።
የእነ ስብሃት ነጋ ቡድን በገሰሰው አየለ ላይ ሲያስፋፉት የነበረውን የስም ማጥፋት ዘመቻ ጥቂቱን እንመልከት፤
  1. ድርጅታችን ተሓህት የገሰሰው አየለ ፊውዳል ድርጅት ነው እየተባለ ነው። ይህንን ግለሰብ ከድርጅቱ ማስወገድ ስላለብን እንተባበር (መለስ ዜናዊ)፣
  2. ገሰሰው አየለ ፊውዳል፣ ጸረ-ትግራይ ትግል በመሆኑ በተመቸው ጊዜ ጠብቆ ተሓህትን ከማጣፋት አይመለስም። የትግራይን ነፃ ሃገርነትና የትግራይን መንግሥት አይቀበልም። ጸረ-ኤርትራ ትግል ነው። የመትከል አገራችን ሻእቢያም  ተማረውበታል። (ስብሃት ነጋ)፣
  3. ኤርትራና ትግራይ የአማራ ቅኝ ግዛት አይደሉም፣ አልነበሩም። ሁሉም የኢትዮጵያ ጥንታዊ ግዛትና አካል ናቸው፣ ስለዚህ የተሓህት ፕሮግራም ውድቅ ነው እያለ እንደ ምስጥ ውስጥ ለውስጥ እየተሽሎከሎከ ከሕዝብ እየነጠለን ነው (ስብሃት ነጋ)።
በዚህ ጊዜ የነበሩ ታጋዮች እንደሚናገሩት ከሆነ በገሰሰው አየለ ላይ በስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ የሚመራው ቡድን የተሰማሩበት የስም ማጥፋት ዘመቻ በየቀኑ ይደርሰው ነበር። በመጨረሻ ተማሮ በህዳር 1968 ከማ/ኮሚቴ ሃላፊነቱ ራሱን አግልሏል። ይህ በመሆኑ በሃዘን እና በቁጭት የሚናገሩ በወቅቱ የነበሩ ታጋዮች ነበሩ። አክራሪውን አመራር ለመቆጣጠር አቅም ነበረን ግን ስህተት ፈጸምን ያሉም አልታጡም።
የዲማ ኮንፈረንስ
የዲማ ኮንፈረንስ የተካሄድው በመጋቢት መጀመሪያ በ1968 ነበር። በዚህ ጊዜ አቶ ገሰሰው አየለ በስብሰባው አልታየም። በወቅቱ በዚህ ጉባኤ የተሳተፉት ታጋዮች ገሰሰው/ስሁል የት ሄደ ብለው ሲጠይቁ የተሰጠው መልስ በሥራ ምክንያት ወደ ሩቅ ቦታ ሄዷል የሚል እንደነበር ይናገራሉ። ኮንፈረንሱ ከመድረሱ በፊት የስብሃት ነጋ ቡድን በአግአዚ ገሰሰ፣ በጥቂቱም ቢሆን በግደይ ዘርአጽዮን ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ አካሂደዋል። ነገር ግን ውጤት አልባ ነበር።
በዲማ ኮንፈረንስ የተመረጡት 1. አረጋዊ በርሄ፣ የተሓህት ሊቀመንበር 2. ስብሃት ነጋ 3. ግደይ ዘርአጽዮን 4. ሥዩም መስፍን 5. አግአዚ ገሰሰ 6. አባይ ፀሃየ 7. ሙሴ (መሃሪ) ተክሌ ነበሩ። ምርጫው ጸረ-ዲሞክራሲ ስለነበር የነበረው አመራር ስብሃት ነጋን መርጦ መለስ ዜንዊን ድምጽ ነሳው። በዚሁ ሁሉም ወደየሥራው ሄደ።
ቀደም ብዬ በአርእስቱ ላነሳሁት ጥያቄ መልስ ለመስጠት፣ የተሓህት – ህወሓት ጸረ-ኢትዮጵያ አካሄድና ዓላማን በመቃወም ለሁለት መሰንጠቁና የሕይወት መስዋእትነት የከፈሉ አመራር ነበሩ ወይ? ከነበሩስ እነማን ናቸው? ለሚለው ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት እነሆ ፎቶግራፋቸውን ከዚህ በማያያዝ አቀርባለሁ።
   ገሰሰው አየለ       አግአዚ ገሰሰ         ሙሴ መሃሪ ተክሌ            አጽብሃ ዳኛው     ዶ/ር አታክልት ቀጸላ
አቶ ገሰሰው አየለ የበረሃ ስሙ ስሁል፣ ተወልዶ ያደገው ሽሬ አውራጃ ነው። ገና በወጣትነቱ የሽሬ አውራጃ ማዘጋጃ ቤት ዋና ሹም በመሆን አገልግሏል። በ1950 አጋማሽ ለፓርላማ ምርጫ ተወዳድሮ በማሸነፍ የኢትዮጵያ ፓርላማ አባል በመሆን ሠርቷል። ለሶስት ተከታታይ ምርጫ በማሸነፍ 15 ዓመት ሙሉ የፓርላማ አባል ነበር። በኢትዮጵያ የተቀጣጠለው አብዮት እየተጠናከረ ሲመጣ በ1966 የማገብት አባል ሆነ።
አቶ ገሰሰው አየለ የማገብትን አላማ፣ ተግባርና ፕሮግራም በጸረ-ኢትዮጵያነት የተሞላ መሆኑን ትኩረት ሳይሰጥ በየካቲት 11 ቀን 1967 ለተመሰረተው የትጥቅ ትግል ግንባር ቀደም መስራች በመሆን በአመራር ደረጃ ግንባሩን ሲመራ ነበር። የተሓህትን ፕቶግራምና ዓላማ ካየ በኋላ ፍጹም ጸረ-ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት፣ ጸረ-ኢትዮጵያ ሕዝብነትን የጨበጠ ፕሮግራምና በፋሽስት ጣልያን የተዘጋጀ ነው እስከማለት ደረሰ። በህዳር 1968 ከአመራሩ ወረደ።
አቶ ገሰሰው አየለ ያነሳው ተቃውሞ ብዙ ቢሆንም ከተራ ቁጥር 1-4 ያሉትን አንኳር ሃሳቦች አስነስቷል። ታጋዩም ድጋፍ ሰጠው። ከአመራሩም እንደነ አግአዚ ገሰሰ፣ አጽብሃ ዳኘው፣ ዶ/ር አታክለት ቀጸላና መሃሪ ከጎኑ ተሰለፉ። በተሓህት ውስጥም ጭንቀትና ሽብር በአመራሩ ወስጥ ተፈጠረ። በስብሃት ነጋ የሚመራው ቡድንም ገሰሰው አየለን በዘዴ ለማጥፋት እቅዱን ዘረጋ።
 የገሰሰው አየለ ደብዛ መጥፋት
ከዲማ ኮንፈረንስ በኋላና ክዛም ትንሽ ቀደም ብሎ ገሰሰው አየለ የውሃ ሽታ ሆኖ ቀረ ሲሉ የት ገባ የሚሉ ታጋዮችም በዙ። በዚህ ጊዜ የተሓህት አመራር እርስ በርሱ የሚጋጭ ወሬዎች በድርጅቱ አሰራጨ።
  1. በአዲ ነብራኡድ ወስጥ በኢዲዩ ወይም ጠርናፊት ድንገተኛ ጦርነት ከፍተው ጠርናፊት ገደለችው፣
  2. እኔ ስለሸመገልኩ አልታገልም ገንዘብ ስጡኝና ሱዳን ሄጄ ልኑር በማለት ገንዘብ ከድርጅቱ ተሰጥቶት በመኪና ተሳፍሮ ሲሄድ በመኪና ውስጥ የነበሩ የኢዲዩ አባላት ገደሉት የሚል ነበር። ሁሉም ውሸት ነው።
    ኢዲዩም ይህንን በተመለከተ ሰፊ መግለጫ በተነ። ገሰሰው አየለን እኛ አልገደልነውም፣ ልንገድለውም አንችልም። የወንድማቻቾች ደም በከንቱ አናፈስም የሚል ሲሆን፣ የገደለችው ተሓህት ናት አሉ።
    በአዲ ነብራኡድ ተገደለ የተባለበት ምክንያት ሕዝቡ ራሱ ምስክርነቱን በሰጠበት በመጋቢት ወር ጦርነት አልነበረም። የደም መፋሰስ አልታየም አለ። የገደሉት ራሳቸው ወያኔዎች ናቸው ሲል ሕዝቡ ምስክርነቱን ሰጠ። አዲ ነብራኡድ የገሰሰው አየለ ቤት ነው። ጊዜው የአቶ ገሰሰው አየለ ስሁል አሟሟት እውነቱ ግልጽ ሆኖ የወጣበት ጊዜ ነበር። ገሰሰው በስብሃት ነጋ የሚመራው የተሓህት አመራር በማይታወቅ ቦታ ደብቀው ወይም እንደ ግዞተኛ አቆይተው በሰኔ 1968 በጥይት ደብደበው ሽላሎ ቡምበት አካባቢ ተገደለ። በግድያው የተሳተፉትም አውአሎም ወልዱና አሰፋ ማሞ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ግን አልታወቁም። ይህንን እውነታ ተከታትለው ሃቁን ያገኙት በተሓህት ወስጥ ለትግል የተሰለፉት የገሰሰው አየለ የቅርብ ዘመዶቹ ናቸው። በጊዜው ሃቁን አስቀምጠው አለፉ። ላደረጉት ጥረት የሚመሰገኑና ባለውለታም ናቸው። ጥቂቶቹ፣ ማለትም እንደነ አዘናው ገ/ጻዲቅ ታፍነው የት እንደገቡ የማይታወቁም አሉ።
    የአቶ ገሰሰው አየለ በተሓህት ፕሮግራም ያስቀመጠው ነቀፌታና ሃሳቡን የደገፉት ግለሰቦች በከፍተኛ ዲግሪ ከቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ የተመረቁ እንደነ እቁባዝጊ በየነ፣ አሰፋ ገብረዋህድ የመሳሰሉ ዘጠኝ ምሁራን የተሓህትን አመራር የውሸት ስም በመስጠት የሥልጣን ሱሰኞች ተብለው ሽራሮ ውስጥ በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። እነዚህም በተሓህት አመራር ቅጥራኛ ባንዳዎች ተገድለዋል። ይሁን እና መልእክታቸውን አስተላልፈው ከዚች ዓለም በግፍ ተገድለው አልፈዋል። ስማቸው ግን አልጠፋም፤ ለዘላለም ይኖራል።
    2.  ዘርኡ ገሰሰ
    ዘርኡ ገሰሰ የበረሃ ስሙ አግአዚ ሲሆን፣ በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ የ4ኛ ዓመት የፖለቲካል ሳይንስ ተማሪ ነበር። ማገብትን ከመሰረቱት አንዱ ነው። በአመራርም እስክ እለተ ሞቱ ተሓህትን ከሚመሩት መካከል ነበር። ዘርኡ ገሰሰና አቶ ገሰሰው አየለ  በተሓህት ፕሮግራም ጠማማነት፣ ጸረ-ኢትዮጵያና ጸረ-ኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑ በሁሉም ነጥብ አይለያዩም፣ አንድ  አቋም ነበራቸው።
    ዘርኡ ገሰሰ የተሓህትን ፕሮግራም አጥብቆ ያወግዘዋል፣ በታጋዩም ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትና ክብርም ያገኘ አመራር ነበር። ይህች ግን ለነስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን እና መለስ ዜናዊ አትዋጥላቸውም። አደገኛ መሪ ብለው ፈርጀው የሚጠበቀው ልክ እንደ ገሰሰው አየለ በዘዴ ማጥፋት ነበር።
    ዘርኡ ገሰሰ በተሓህት ፕሮግራም በገጽ 8 ላይ የሰፈረውን እና ሌላውን ፕሮግራም ሁሉ አደገኛ ስለሆነ ፈጽሞ መወገድ አለበት በማለት ከብዙ አመራሮች ጋር መነጋገሩ የቅርብ ሰዎች የሚሉት ሃቅ ነበር። ነገር ግን ሰሚ አላገኘም። እነ ስብሃት ነጋ የሚገደልበትን ዘዴ ለማመቻቸት ይሯሯጡ ነበር።
    አግአዚ ገሰሰ ከግደይ ዘርአጽዮን እና ከአረጋዊ በርሄ ጋር ጥሩ ግንኙነት እንደነበራቸው የሚያውቁ ታጋዮች በዚሁ ሴራ ሁለቱ ምንም ዓይነት ተሳታፊነት አልነበረባችውም የሚሉም ብዙ ናቸው። የሴራው አካላት ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን፣ አውአሎም ወልዱና ስየ አብርሃ ናቸው በማለት ያረጋግጣሉ።
    ይህ በእንዲህ እያለ የተሓህት አመራር ስብሃት ነጋና አባይ ፀሃየ ሆነው ዘዴውን አቀነባብረው ከጨረሱ፣ አግአዚን ጨምሮ በአክሱም ከተማ ትልቅ ሥራ እንዳለ አስመስለው ሃሳባቸውን በማቅረብ የሚፈጸመውም በአመራር ደረጃ ስለሆነ አግአዚ ተዘጋጅ ብለው በትንሽ ቀናት እንደሚገናኙ ተወሰነ። ስብሃትና አባይ ፀሃየ ጠላት በብዛት የሚገኝበት ለመንቀሳቀስም ሆነ መንገዱን መጠቀም በማይቻልበት ቦታ ወቅሮ ማራይ መሆኑ በሕዝብ ግንኙነት ጥናት አግኝተዋል። ወቅሮ ማራይ በደርግ ሚሊሺያ የታጠረ ነው። ቀኑ ደረሰ፣ አግአዚ ገሰሰና ነፃነት ሰንደቅ አብረው ከነስብሃት ጋር ሰመማ በሚባል ቦታ ተገናኙ። ስብሃት ነጋ ለአግአዚ በየትኛው ቦታ ለመሄድ አስበሃል ሲለው በመደባይ ታብር በኩል ሲለው የመረጥከው መንገድ አደገኛ ነው በማለት በሕዝብ ግንኙነት አጥንተን ወቅሮ ማራይ ነፃ መሆኑን፣ ሚሊሻም ሆነ የደርግ ሰራዊት የሌለበት ነው ካሉት በኋላ በህሳቡ ተስማምተው መንገዳቸውን ቀጠሉ። ነፃነት ሰንደቅ አብሮት ስለነበረ ሁሉንም ሰምቶታል። ወቅሮ ማራይ እንደገቡ በሚሊሻ ተከበው በተተኮሰ ጥይት አግአዚ ገሰሰ ወዲያውኑ ወድቆ ሞተ። ነጻነት ግን አመለጠ። እንደምንም ብሎ ዘና ወረዳ ገባ። እዛ ላገኛቸው ታጋዮች የደረሰባቸውን ሲነግራቸው፣ ነፃና ጥሩ መንገድ ነው ብለው ስብሃትና አባይ ፀሃየ አግአዚም የተናገሩትን አምኖ በሚሊሻ ተከበን የጥይት ናዳ ወርዶብን አግአዚን ገደሉት፣ እኔ አመለጥኩ። ስብሃት ነጋና አባይ ፀሃየ ባዘጋጁት የግደያ ዘዴ የሚቃወማቸውን አግአዚ ገሰሰውን አጠፉት ብሎ የተናገረው በተሓህት ውስጥ ተሰራጨ። ስብሃትና አባይ ተከታትለው ነፃነትን ለማግኘት የተፈጠረው ነገር ለማንም እንዳይነገር አስጠነቀቁ። ሆኖም ግን ነገሩ ተሰራጭቷል። አመራሩም የአግአዚን ሁኔታ አንዲት ቀንም ሳያነሳ ቆይቶ በ1ኛው ጉበኤ በጠላት ተገደለ ብለው ተናገሩ። የስብሃት የግድያ ሴራም ሰመረለት።
    3.  መሃሪ ተክለ
    መሃሪ ተክለ የበረሃ ስሙ ሙሴ ነው። በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ሲማር የቆየ፤ ከሻእቢያ ጋር የተሰለፈ የሻእቢያ ታጋይና አመራር የነበረ ሰው ነው። ሻእቢያና ማገብትን በማይበጠስ የብረት ሰንሰለት ያቆራኘው መሃሪ ተክሌ ነው። ማገብትን የመሰረቱት እነ አረጋዊ በርሄ በጥር 1967 ሳህል ኤርትራ በረሃ ወርደው በሻእቢያ ወታደራዊ ትምህርት ሰልጥነው ብረት ታጥቀው ደደቢት በረሃ እንዲወርዱ ትልቅ ሚና የተጫወተው መሃሪ ተክሌ ነው። መሃሪ ተክሌ በሻእቢያ ተፈቅዶለት በተሓህት ውስጥ እንዲታገል ደደቢት በረሃ ከነ አረጋዊ በርሄ ተቀላቅሎ የተሓህት ተዋጊም ሆነ።
     የሙሴ ያልተጠበቀ የአቋም ለውጥ
    ሙሴ የሁሉንም ታጋይ ባህሪ ጥናት ለመውሰድ ጥቂት ወራቶች ቢወስድበትም የተሓህት ታጋይ ለምንም ለውጥ ዝግጁ መሆኑን አወቀ። የእነ ገሰሰው አየለ አግአዚ ወዘተ. በተሓህት ፕሮግራም ላይ ያላቸውን አመለካከት አወቀ። ከአስገደ ገ/ሥላሴም ጋር ጥሩ ግንኙነት መሰረተ። ታጋዩና ሙሴ ውህደት ፈጠሩ፣ ወደዱትም። በዲማ ኮንፈረንስ ለአመራር ብቁ ነው ብሎ ታጋዩ ወደ ተሓህት መሪነት አደረሰው። ም/ወታደራዊ አዛዥም ሆነ። ይህ በወቅቱ ለነበረው ታጋይ ታላቅ ድል ነበር።
    ሙሴ ባልተጠበቀ ሁኔታ ጸረ-ሻእቢያ አቋም ያዘ። ሻእቢያ ጸረ-ሕዝብ፣ በተለይ ደግሞ ጸረ-ትግራይ ሕዝብ ነው። ሻእቢያ የኔ ጠላት የትግራይ ሕዝብ ነው የሚል አክራሪ ድርጅት ነው፤ የተሓህት አመራር ደግሞ ሻእቢያን እንደፈጣሪ እየቆጠሩ ጠዋት ማታ እግሩን ይስማሉ በማለት በተጠናከረ መልኩ ጸረ-ሻእቢያ ቅስቀሳውን በማቀነባበር በስፋት ቀጠለበት፣ ታጋዩም አብሮት ቆመ።
    አመራሩም ሙሴ ከመትክል የትግላችን አጋር ሻእቢያ እየለያየን ነው በማለት ሲናገሩ፣ በእንጻሩ ሙሴ ነፃ ሁኑ፣ አሽከር አትሁኑ፣ የሻእቢያ አገልጋይና ታዛዥ አትሁኑ ነው የምላችሁ ሲላቸው የተሓህት አመራር ሙሴን ማውገዙን ቢቀጥሉበተም በታጋዩ ተቀባይነት አላገኘም። ይበልጡኑ የሙሴ ተቀባይነት ከፍ አለ። በዚህ ምክንያት አመራሩ ሙሴ መሃሪ ተክሌ የሚጠፋበትን መንገድ ማጠንጠን ጀመሩ። የግድያ ሴራ በስብሃት ነጋ የሚመራው የመለስ ዜናዊ፣ አባይ ፀሃየና ሥዩም መስፍን በመተባባር እቅዱን አወጡ። ተግባር ላይ የሚያውሉት ደግሞ ስየ አብርሃና ጻድቃን ገብረተንሳይ ሲሆኑ ግድያውን የሚፈጸመው በርሄ ሃጎስ ሆኖ ተመረጠ። በርሄ ሃጎስ አሁን ካናዳ፣ ኦቶዋ በመኖር ላይ ያለ ግለሰብ ነው። በላፈው ግንቦት 2005 አማራው የትግራይ ሕዝብ ጠላት ነው እያለ አማራውን ኢትዮጵያዊ ሲሰድበውና ሲያንቋሽሸው የነበረ ሰው ነው። በገዘ ተጋሩ ፓል ቶክ።
    ስየ አብርሃ በሚመራት ሃይል 41 አመቺ ጊዜ ሲጠብቅበት የነበረው ሙሴ ጻድቃን ገብረተንሳይ በኮሚሳርነት የሚመራት ጋንታ በርሄ ሃጎስ የነበረባት ጋንታ በመጠባበቅ ላይ የነበሩት ሁለቱ በአጋጣሚ ሓምሌ መጨረሻ 1968 ከሽራሮ ወጣ ብላ የምትገኘው ቁሽት ጫአ መስከበት ስየ አብርሃ ም/ሃይል መሪ በያዛት ሃይል በኢዲዩ ላይ ጥቃት እንደተጀመረ፣ ሙሴ ታጋዮቹን እያስተባበረ ጦርነቱን በመምራት ላይ እንዳለ በስተኋላው የነበሩት ጻድቃን ገ/ተንሳይና በርሄ ሃጎስ ውጊያው እየበረታ ሲሄድ በርሄ ሃጎስ አነጣጥሮ ሙሴ (መሃሪ) ተክሌን ግራ እጁ ላይ ትከሻውን ጨምሮ ቆርጦ ጣለው። ዞር ሲል ጻድቃን ገ/ተንሳይና በርሄ ሃጎስ ከኋላ ሆነው እንደመቱት አወቀ። አይን ለአይንም ተገጣጠሙ። በርሄ ሃጎስ ሙሴን የመታበትን ደምመላሽ ጠመንጃም ለጻድቃን ሲሰጠው አየው። ክፉኛ የቆሰልውን ሙሴን በቃሬዛ ተሸክመውት ሲሄዱ የነበሩትን ታጋዮች ሁሉ የነገራቸው እኔ በኢዲዩ ጥይት አልተመታሁም፤ የመቱኝና የገደሉኝ ጻድቃን ገብረተንሳይና በርሄ ሃጎስ ናቸው እያለ ሲናገር እንደነበረና አንድ ሰዓት ተኩል ያህል ቆይቶ ከዚች ዓለም እንደተሰናበተ ይናገራሉ። አዲ ፀጸር ቀሽት ወስጥ ተቀበረ። ወዲያው በርሄ ሃጎስ ትንሽ ገንዘብ ተቀብሎ ሱዳን ገባ። ሙሴ  የተናገረውን ኑዛዜ አውአሎም ወልዱ ሰምቶታል፣ ምስክርነቱን ይስጥበት።
    4.  አጽብሃ ዳኘው
    አጽብሃ ዳኘው፣ የበረሃ ስሙ ሸዊት ነው። በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ በሂሳብ ትምህርት የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ነበር። ማገብት እንደተመሰረተም ከወራት በኋላ አባል ሆነ። መጋቢት 1967 ከተሓህት ጋረ ተቀላቀለ።  ከጊዜ በኋላም በተሓህትን ፕሮግራም አደገኛነት ሂስ መሰንዘር በመጀመር ፕሮግራሙ ጸረ-ሃገር ሉአላዊነት፣ ጸረ-ኢትዮጵያ ሕዝብና በታኝ፣ ሕዝብን እርስ በርሱ ለግጭት የሚዳርግ በመሆኑ አዲስ ፕሮግራም ማርቀቅ ይጠበቅብናል በማለት ከነ ገሰሰው አየለ – አግአዚ ገሰሰ ጋር በአቋም ተስማሙ። በሚሰነዝረው ሃሳብ በታጋዩ ተወዳጅ ሆነ፣ በድፍረቱም ምክንያት ስሙ ገነነ። በዚህ መልክ ሲቀጥል፣ ሱዳን፣ ካርቱም ለሥራ ሂዶ በነበረበት ወቅት መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ በአስቸኳይ አስጠርተው ሱዳን ባለህበት ጊዜ ጾታዊ ግንኙነት ፈጽመሃል በማለት በውሸት ከሰው 06-ሃለዋ ወያነ አስገብተው አሰሩት። አረጋዊ በርሄ ይህን እንደሰማ ከነበረበት ቦታ በቶሎ ደርሶ ከእሰር አስወጥቶ ሥራውን እንዲቀጥል አደረገ። ሐምሌ 1968 አመራሩ ወደ አምስት ስለወረደ ገሰሰው አየለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሴ (መሃሪ) ተክሌ በተሓህት አመራር ስለተገደሉ፤ በአመራር ላይ የቀሩት አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሃየ ብቻ ነበሩ። ከላይ በጠቀስኩት ወርና ዓ.ም. አምስቱ አመራር ተሰብስበው የሚከተሉት ወደ አመራሩ ገቡ። መለስ ዜናዊ፣ አጽብሃ ዳኘው፣ አውአሎም ወልዱና ስየ አብርሃ ወደ ተሓህት አመራር ወጡ።
    አጽብሃ ዳኘው ለስልጣን እና ሹመት እጁን አልሰጠም። የተሓህት ፕሮግራም ጸረ-ኢትዮጵያና ጸረ-ሕዝብ፣ አውዳሚና በታኝ ስለሆነ መወገድ አለበት፣ ተሓህት ጠባብና ዘረኛ ስለሆነ ትግላችን ኢትዮጵያዊ መሆን አለበት። ትግራይ የአማራ ቅኝ ግዛት ናት፣ አማራ ጠላት ነው ማለት ሕገወጥ የፖለቲካ አቋም ነው በማለት ተከራከረ። ክርክሩን እገላ ወረዳ ስብኦ ቁሽት ሲከራከሩ ስብሃት፣ መለስና አባይ ተናደዱ። ሆያ አዲጨጓር የሚገኘው 06-ሃለዋ ወያነ ሃላፊዎች፣ ሙሉጌታ አለምሰገድና ክንፈ ገ/መድህንን አስጠርተው ዛሬውኑ አጽብሃ ዳኘውን እና ጓደኛው መኮንን በዛብህን ግደሏቸው። ስብሃት ነጋ ጸረ-ተሓህት ናቸው የሚል ወረቀት ጽፎና አዘጋጅቶ ሰጣቸው። እነአጽብሃ መኮንን የተሰጣቸውን ወረቀት ይዘው በመሄድ ሆያ ላይ ጉድጓድ ተቆፍሮ በጥይት ተደብድበው በመገደል ከዚህ ዓለም ተሰናበቱ።
    አረጋዊ በርሄ የአጽብሃ ዳኘውና የመኮንን በዛብህን መታሰር ሰምቶ ከነበረበት ተምቤን አካባቢ ሌት ተቀን ተጉዞ ሕይወታቸውን ለማዳን ያደረገው ጥረት የሚያስመሰግነው ነው። ሆያ እንደገባ እነ አጽብሃ ወደኔ አምጡልኝ፣ ተፈትተዋል፣ ጥፋት የለባቸውም ሲል ከሙሉጌታ አለምሰገድ ጋር ያገኘው መልስ፣ ስብሃትና መለስ አባይ ሆያ እንደገቡ ሳይውሉ ሳያድሩ ይገደሉ ብለው ስላዘዙን ገደልናቸው አለው። የትእዛዝ ወረቀቱም የኸው ብሎ ሰጠው። አረጋዊ በርሄ ይህንን አሳዛኝ ግድያ ሰምቶ እነስብሃት ነጋ ወደሚገኙበት እገላ ሰብኦ፣ ቁሽት በመሄድ ተገናኛቸው። ነገር ግን ምንም አላደረገም። የተሓህት ሊቀመንበር እንደመሆኑ ለምን ይሆን በነስብሃት ነጋ፣ መለሰ ዜናዊ ወዘተ. ላይ እርምጃ ሳይወሰድ የቀረው የሚል ጥያቄ ተነስቶ ነበር። አሁንም እየተነሳ ነው። መልስ መስጠት ያለበትም የወቅቱ የተሓህት ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄ ነው።
     5.  ዶ/ር አታክልት ቀጸላ
    ዶ/ር ራስወርቅ ቀፀላ የበርሃ ስሙ ዶ/ር አታክልት ቀፀላ የህክምና ባለሙያ ነው። ቀደም ሲል ከግንባር ገድሊ ሓርነት ትግራይ (ግገሓት) አባል ሆኖ በረሃ ሲንቀሳቀስ የግገሓት የትግል ስልት አደገኛ ነው በማለት በሰኔ 1967 ከተሓህት ተቀላቀለ። በተሓህትም ብዙ ስህተቶች እንደሚኖር አልተጠራጠርም ነበር። ነገር ግን ስህተቱን ለማስተካከልና ለማረም ብዙ ታጋዮች ይኖራሉ የሚለው እምነቱን እንደያዘ ቀስ በቀስ ፕሮግራሙን የማየት እድል ገጠመው። ከነገሰሰው አየለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሴ መሃሪና አጽብሃ ዳኘው ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለፈጠረ፣ እነዚህ ሁሉ የተሓህት ፕሮግራምን የሚቃወሙ ናቸው። አጽብሃ ዳኛው በነስብሃትና መለስ እንደተገደለም ዶ/ር አታክለት ቀጸላ በአጽብሃ ፈንታ የተሓህት አመራሩን ጨበጠ። ግን እጁን አልሰጠም።
    ዶ/ር አታክለት በፕሮግራሙ መጥፎና አደገኛ፣ ሃገርንና ሕዝብን የሚበታተን ነው ብሎ በማመን ከተለያዩ አመራር ጋር ሲነጋገርበት እንደነበር ይታወቃል። ከግደይ ዘርአጽዮን እና አረጋዊ በርሄ መግባባት እንደነበረውም ራሱ የተናገረው ነው።
    ከመለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየና ከሌሎቹ አመራር ጋር ግን የሻከረ ግንኙነት እንደነበረው ታጋዩ ሁሉ ያውቃል። ሌላው ቀርቶ ስብሃት ነጋ በየቦታው በሄደበት “የኢትዮጵያ ባንዲራ ራሱ ላይ ጠምጥሞ ዶ/ር አታክለት ቀጸላ በድርጅታችን ተሓህት ችግር እየፈጠረብን ነው” በማለት በየቦታው መናገሩን እኔ ራሴ አስታውሳለሁ። ዶ/ር አታክልት ቀጸላ በ1ኛው ጉባኤ የተሓህት የአመራር ምርጫ በከፍተኛ የድምጽ ቁጥር ተመርጦ የህወሓት ማ/ኮሚቴና ም/ወታደራዊ አዛዥ ሆነ። የነስብሃት ነጋ የስም ማጥፋት ዘመቻ አልተሳካም። በነገሩም ተደናግጠው ነበር።
    ይህ በየካቲት 5 ቀን 1971 በአዲነብር ኡድ ወረዳ ማይ አባይ በተባለው ቦታ የተካሄደው 1ኛ ጉባኤ፣ የተሓህት ውርስ ስብሃት ነጋ ሊቀመንበር የሆነበት ጉባኤ ወርሱን የተረከቡት ስብሃት ነጋና ህወሓት ናቸው። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ቀደም ብሎ የመጣው ፋሽስት ቡድን እውቅና ያገኘበት ጊዜ ነበር።
    እነስብሃት ነጋ ዶ/ር አታክልትን ለማጥፋት ብዙ ጥናት በማካሄድ የተመቸ ጊዜ አገኙ። ግንቦት 1971 የውጊያው ዓይነት ጥቃት በኢትዮጵያ ሰራዊት፣ የውጊያው ቦታ ተምቤን፣ አብይ አዲ ጎንባስ ሞሞና ነበር። የህወሓት ሰራዊትም ይዘጋጅበት ነበር። ቀኑ ደርሶ ሁሉም የህወሓት ሰራዊት ወደ ውጊያው ቀጠና አመራ። ውጊያው የሚጀምርበት ጠዋት በስተምእራብ በኩል ከውጊያው ቦታ በግምት በ10 ኪ.ሜ. ርቀት ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየና ሳሞራ የኑስ፣ የታጠቀው መሳሪያ ሲሞኖቭ ባለመነጽር ሆነው ዶ/ር አታክልት ቀጸላን የህወሓት ሊቀመንበር ስብሃት ነጋ ስለጦርነቱ ለመነጋገር ብሎ አስጠራው። እነሱም ለግድያው በመዘጋጀት በጠሩት መሰረት ደረሰ። ፊታቸውን ወደ ውጊያው ቀጠና ምስራቅ በማዞር ቀስ እያሉ መንገዱን ቀጠሉ። እኔና ዶ/ር አባዲ መስፍን ከነስብሃት ነጋ ፊት 500 ሜትር ያህል በሚገመት ርቀት ወደ ጦርነቱ ቀጠና እንጓዝ ነበር። ዶ/ር አታክለት ቀጸላ ስብሃት ነጋ እንዳሰናበተው በፍጥነት እየተጓዘ ሳለ ከ250-300 ሜትር ርቀት ከነሱ መካከል ሳሞራ የኑስ በያዘው ሲሞኖቭ ባለመነጽር ጠመንጃ አስተካክሎና አነጣጥሮ በመተኮስ ዶ/ር አታክልት ቀጸላ የጀርባው አከርካሬ ላይ መታው። ‘Special Column’ ተመትቶ ሲወድቅ አዩት። አባይ ፀሃየ በፍጥነት ሩጦ ወደኛ ተጠግቶ አባዲ፣ አባዲ፣ ብሎ በመጥራት በእጅ ምልክት ኑ ሲለን ሄደን አገኘነው። ዶ/ር አታክልት ስለሞተ ቅበሩት፣ ነገር ግን ለማንም እንዳትናገሩ ብሎ ተመልሶ ከነስብሃት ነጋ ጋር ተቀላቀለ። በኋላም ሶስቱም ተያይዘው ሲሄዱ አየናቸው።
    ዶ/ር አባዲ መስፍን እና እኔ ጉድጓድ ስንቆፍር እሱ እንደ ባለሙያነቱ ሬሳውን መመርመር ጀምረ። ጀርባው ላይ የመታችን ጥይት ሰውነቱን ከፍቶ አወጣት። በሲሞኖቭ ጥይት ሳሞራ የኑስ ገደለው ብሎ እምባውን መግታት አቃተው። ጥይቷን በወርቀት ጠቅልሎ ያዛት። እኔና ዶ/ር አታክልት አፈርና ድንጋይ በመጫን ቀብረን ተሰናብተን ወደ ጦርነቱ ተመለስን። ዶ/ር አታክልት ሞቶ ይቀበር እንጂ ታሪኩ ህያው ህኖ ይኖራል። እነ ስብሃት ነጋ መለስ ዜናዊ ወዘተ. በንጹሃን ደም መታጠብ የጀመሩት ገና ከጥዋቱ ነበር። እነዚህ ጀግኖች በሞት ቢለዩንም ድምጻቸውና የተቀደሰ ተቃውማቸው፣ የህወሓት ፕሮግራም ይውደም ያሉት ድምጻቸው ግን በታጋዩ ዘንድ ተሰራጨ። በዚህም ምክንያት ብዙ ዲሞክራሲያዊ ጥያቄዎችን በማንሳት የተሓህት- ህወሓት አመራርን አስጨነቁት። አመራሩ ተቃውሞውን አጠፍ በማድረግ በድርጅታችን ሕንፍሽፍሽ ተነሳ ብሎ ብዙ ታጋዮችን እና ንጹሃንን መጨፍጨፊያ ምክንያት አደረገው። የዲሞክራሲ ጥያቄው ተዋንያኖች፤ ገሰሰው አየለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሴ መሃሪ፣ አጽብሃ ዳኘውና ዶ/ር አታክልት ቀጸላ ያቀጣጠሉት ነው። የህወሓት ፋሽስትና አምባገነን መሪዎች የመጥፊያቸው ጊዜ እየቀረበ ነው፣ ተያይዘው በሕዝብ ሃይል ለፍርድ ይቀርባሉ።
     6. ግደይ ዘርአጽዮን
    ግደይ ዘርአጽዮን ከአረጋዊ በርሄ ጋር በመሆን የማገብት-ተሓህት-ህወሓት የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጡ ህወሓትን የፈጠሩት ሁለቱ ናቸው። ሌላ የለም። ግደይ የተፈጸሙ ጥፋትም ሆነ ወንጀል ካሉ ከነበሩት አመራር እኩል ተጠያቂ ነኝ በማለት በግልጽ ተናግሯል። በህወሓት አመራር አስከቆየሁበት በተፈጸሙ ወንጀሎች ተጠያቂ ነኝ። ነጻ ነኝ ብሎ ራሱን ያላገለለ በመሆኑ ያስመሰግነዋል።
    ግደይ ዘርአጽዮን የተሓህት-ሀወሓት ከፍተኛ አመራር የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር በነበረበት ጊዜ አመራሩ የሚፈጽመውን ግድያና ሽብር አውግዞ ከ1969 መጨራሻ ራሱ ነፃ በመሆን የስንት ታጋይና ሰላማዊ ዜጋ ሕይወት ያዳነ ነው። ግን ብቻውን በመሆኑ የህወሓትን አመራር ክሚፈጽሙት ወንጀል ሊያቆማቸው አልቻለም። በሰላማዊው ዜጋና በታጋዩ ግን ሰፊ የታማኝነት፣ አጋርነትና ክብር የተሰጠው ግደይ ዘርአይጽዮን ነው። ግደይ የታጋዩ ጥብቅ ጓደኛ ሆነ፣ ተወደደ። ማንኛውም ታጋይ ችግር ሲገጥመው ለግደይ ያናገራል። ግደይም ችግሩን ይፈታለታል። ግደይ ራሱም የታጋዩን እና የሕዝቡን ፍቅር ጣእሙን ስላወቀው ሁልጊዜም ደስተኛ ነበር።
    መለስ ዜናዊ የሚመራውን ማርክሲስት ሌሊኒስት ሊግ ትግራይ ለማቋቋም የሃላፊነቱ ተሰጠው። በ1ኛው ጉባኤ በኮሚሽን ደረጃ እንደተቋቋመ በአቋም ልዩነታቸው እነ መለስ ዜናዊ፣ ግደይን እንደጠላት ማየት፣ ግደይ ዘርአጽዮንም በአቋሙ ስለጸና መፋጠጥ የጀመርንበት ጊዜ ነበር። የነበራቸው ልዩነትም የማይፈታ ሆነ። ሁለቱም በተጻራሪ መንገድ ቀጠሉበት።
    በእነ መለስ ዜናዊና አበሮቹ የሚያቀርቡት፤     
    ብሄራዊ ዲሞክራሲያዊ አብዮት የአብዮቱ መሰረታዊ ሃይሎች ድሃ ገበሬ፤ ላብ አደሩ ሲሆኑ፣ እነዚህን ካሰባሰብን የአብዮቱ ትግል ዓላማው እና ግቡን ይመታል። ሃብታም ገበሬ ከሁለት ጥንድ በሬዎች በላይ ያሉት ሃብታም ገበሬ ስለሆነ በማርክስ ሌኒናዊ ሳይንስ ሃብታም ገበሬ የትግላችን ጠላት ነው፣ በማለት አስረግጠው ተናግረዋል። ሃብታም ገበሬ መደምሰስ መጥፋት አለበት። ለምን የማርክስ ሌኒናዊ ጠላት ሃብታም ገበሬ ነው። መለስ ዜናዊ ይህንን በወይን መጽሔት እያተመ ታጋዩን ያስተምርበት ነበር።
    ግደይ ዘርአጽዮን
    ሃብታም ገበሬ የማርክሲዝም ሌኒኒዝም ጠላት አይደለም። አሁንም በህወሓት የሚመሰረተው ማርክሲስት ፓርቲ ሃብታም ገበሬ ጠላት ሳይሆን የትግል አጋራችን እና ወዳጃችን ነው ተብሎ በትግሉ እንደ ወዳጅ መታወቅ አለበት። ከሁለት ጥንድ በሬ በላይ ያለው ሃብታም ገበሬ ነው ስለሆነም ጠላት ነው እያላችሁ ምክንያት በመፍጠር ያምታጠቁት የትግራይ ሕብረተሰብ ፍጹም ጸረ-ሕዝብ ነው። ንብረቱ ሁሉ እየተወረሰ ለህወሓት ገቢ ሲደረግ ለተገደለው ሕዝብና ለፈረሰው ቤት ተጠያቂ ናቸው። ይህ የሃሳብ ልዩነት በነመለስ ዜናዊ ቡድን እና በግደይ ዘርአጽዮን መካክል ሰፍቶ በመውጣት ለዓመታት ቀጠለ።
    መለስ ዜናዊ
    በእኛና በግደይ ዘርአጽዮን መካከል ሰፊ ልዩነት አለ። አብረን መታገልም አንችልም። ግደይ ዘርአጽዮን ሃብታም ገበሬ የማርክስ ሌኒናዊ የትግል አጋር ነው፣ ጠላት አይደለም ብሎ ያምናል። ይህ የሚያመለክተው ግደይ ዘርአጽዮን ጸረ-ማርክስ-ሌሊናዊና በራዥ ነው ሲል በያዘው አቋም የማይነቃነቀው ግደይ፣ አንተና ጓደኞችህ ናችሁ በራዥና ከላሽ ነህ ስለአለው ንትርኩ ሰማይ ወጣ። ግደይ ዘርአጽዮን አሁንም በዚህ ጉባኤ አቀርበዋለሁ። ሃብታም ገበሬ የትግላችን አጋርና ወዳጅ መሆኑ ሙሉ እምነቴ ነው። ሃብታም ገበሬ ጠላት ነው ብሎ ማስቀመጥ ጸረ-ሕዝብ ነው። እነ መለስ ዜናዊ ሃብታም ገበሬ ጠላት ነው ማለታቸው ማንነታቸውን በትክክል ይገልጸዋል።
     2.  በማለሊት ጉባኤ አመራሩ ዳግም ለሁለት መሰንጠቅ
    የማለሊት ጉባኤ በዚህና በሌላውም ጸረ-ዲሞክራሲ ሲካሄድ ሰንብቶ ሐምሌ 21 ቀን 1977 ምርጫው ደረሰ። ይህ ምርጫ ሕገወጥነትን የተከተለና ሁለት ዋና ዋና ዓላማ የያዘ ነበር።
    1. የሥልጣን ሽኩቻ ዋና ዓላማው ነበር፣
    2. በዚህ የሥልጣን ሽኩቻ ማገብት-ተሓህት-ህወሓት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠው በጸረ-ዲሞክራሲና በጸረ-ሕዝብነቱ አብረው እየመሩት የመጡት አንጋፋ አመራሮች ለማባረር በድርቅ የተጠቃው መከረኛው የትግራይ ሕዝብ እያለቀ ከአፉ ነጥቀው በነስብሃት ነጋ፣ በስንት ሚሊዮን ብር የተዘጋጀው ማለሊት ስልጣናቸውን ለማደላደል ነበር።
    ምርጫው
    በሙሉ ድምጽ የመራጭ ብዛት 250 ነበር። ምርጫው በምስጢር ሆኖ በወረቀት የምትፈልገውን መምረጥም ነበር። ምርጫው ተካሄደ። ድምጹ ተቆጠረ። በዝርዝር ተነገረ። 1ኛ. ግደይ ዘርአጽዮን፣ ያገኘው ድምጽ 247፤ 2ኛ. አረጋዊ በርሄ፣ ያገኘ ድምጽ 245፤ 3ኛ. ሃየሎም አርአያ፣ ያገኘው ድምጽ፣ 236፤ 4ኛ. ስየ አብርሃ ወዘተ. እያለ የድምጽ ቆጠራው ቀጠለ። ወደ መጨረሻው ድምጽ ቆጠራ ደረሰ። ይህንን የሚገልጸው ህብሩ ገብረኪዳን ነበር። በጥቁር ሰሌዳ ላይ የተመረጡት ያገኙትን ድምጽ እየጻፈ ሲገልጽ የሚይዘው የሚጨብጠውን አጣ። የጉባኤው ተሳታፊ ቀጥል ብሎ አፋጠጠው። ላብ ፊቱ ላይ እየወረደ ቀጠለ። 24ኛ. መለስ ዜናዊ፣ ያገኘው ድምጽ 130፤ 25ኛ. ስብሃት ነጋ፣ ያገኘው ድምጽ 127 በማለት የ25ቱን የማለሊት ተመራጮች የማለሊት ማ/ኮሚቴ ብሎ በጥቁር ሰሌዳው ላይ በማስቀመጥ ተመልሶ ወደ ቦታው ሄዶ ተቀመጠ። መለስ ዜናዊ ራሱን ደፋ። ፊቱ የተጠበሰ ስጋ መሰለ። ስብሃት ነጋ ደግሞ አዳራሹን ለቆ ወጣ። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የጉባኤው ሊቀመንበር የነበረው ሥዩም መስፍን ከሰዓት በኋላ በ11 ሰዓት እዚህ እንገናኝ ብሎ ጉባኤተኛውን አሰናበተ። በዚህ ዓይነት ነበር ታጋዩ እነ መለስ ዜናዊን መሬት ውስጥ የቀበራቸው። ነገር ግን ተመልሰው ታጋዩን አጠቁት። ብዙ ነባር ታጋይ በእነ መለስ፣ ስብሃት ወዘተ. ተገደለ፣ ከሞት የተረፈውም ሸሸ።
    ልክ በ11 ሰዓት ጉባኤው ተሰየመ። በስብሃት ነጋ አመራር የተመረጡት ማ/ኮሚቴ ማለሊት አሰባስቦ ሹመትና ሥልጣን እየሰጠ እንዲተባበሩት አደረገ። ከአረጋዊ በርሄ ስልጣን አገኛለሁ ብሎ ስየ አብርሃ በከፍተኛ ድምጽ የመረጥነው በግንባር ቀደምትምነት ክህደት ከነ ስብሃት ጋር ተሰለፈ። በዚሁ ጉባኤ የመጀመሪያው ተናጋሪ መለስ ዜናዊ፤ ቀጥሎ ስብሃት ነጋ፤ ቀጥሎ ስየ አብርሃ በመተባበር ግደይ ዘርአጽዮን እና አረጋዊ በርሄ ከህወሓት ከማለሊት ተባረዋል ተባለ። ታጋዩ ተደናገጠ፣ አጉረመረመ አለቀሰ። ከአመራሩ ጻድቃን፣ ሥዩም ገብሩ፣ ወዘተ. በየተራ በሁለት አንጋፋ አመራር አሰነዋሪ የሆነ ስድብ አወረዱባቸው። የተባረሩትም ክኛ ጋር ተቀላቀሉ። እነ መለስ ዜናዊ ተደላድለው በህወሓት-ማለሊት ኮርቻ ላይ ተቀመጡ። የህወሓት ሁለተኛ መሰንጠቅ ይህ ነው።
    የስየ አብርሃ ክህደት
    ስየ አብርሃ ደፋርና ጎበዝ እንደነበረ አውቃለሁ። ከሃዲነቱን ግን አላውቅም ነበር። በ1969 የሕንፍሽፍሽ ዋና ተዋናይ ነበር ተብሎ በስብሃት ነጋ የሚመራው ቡድን እስከ 1977 ድረስ በዓይነ ቁራኛ ሲከታተሉት እንደነበር አውቃለሁ። ከህወሓት ታጋዮች ደግሞ ለሰየ አብርሃ ጥብቅና እና ድጋፍ አልተለየውም ነበር። ከዚህም የተነሳ ነው በማለሊት ጉባኤ በከፍተኛ ድምጽ የመረጥነው። ነገር ግን ከሃዲውና እምነተ ቢሱ ስየ አብርሃ የሥልጣን ጥማቱን ለማርካት የህወሓት-ማለሊት ሙሉ ወታደራዊ አዛዥ ለመሆን ግደይ ዘርአጽዮንን እና አረጋዊ በርሄን በውሸትና በስም ማጥፋት ደበደባቸው። ሲጠብቀውና ሲንከባከበው የቆየውን ታጋይ ለምን መለስ ዜናዊን እና ስብሃት ነጋን በአነስተኛ ደምጽ መረጣችሁ ብሎ ነባሩን ታጋይ እንደ እባብ እራስ እራሱን ቀጠቀጠው። በየቦታው እየሄደ አጠፋው።
    በህዳር 1980 የህወሓት ታጋይ ባነሳው ተቃውሞ ኤርትራም ሆነ ሌላ ቦታ ሂደን አንዋጋም። ትግራይን ከአማራው ቅኝ አገዛዝ ነፃ አውጥተን የትግራይን መንግሥት መመስረት ነው እንጂ ከዚህ ውጭ የምናውቀው ነገር የለም። ኤርትራ ሄደው በረሃ የበላቸውና ያለቁት የትግራይ ወጣት ሴትና ወንድ እስከ አሁን 130,000 ደርሷል። የኛ ድርጅት ህወሓት ከየት ወረዳና ዞን መጡ የሚል ዝርዝር ስማቸው እንኳን አያውቀውም። እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ከብት እየታፈስን ሂደን ሞተን ቀረን። አሁንም ትግራይን ነፃ እናወጣለን እንጂ ሌላ ቦታ አንሄድም አለ። በዚህ ጊዜ እነ መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ስየ አብርሃን አነጋግረው በ36,000 ታጋይ ላይ ሞት ፈረዱበት። ይህ ሁሉ ታጋይ የውሃ ሽታ ሆኖ ቀረ። በዚህ ግድያ የተሰማሩት መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ሃየሎም አርአያ፣ ሳሞራ የኑስ፣ ጻድቃን ገ/ተንሳይ፣ አበበ ተክለሃይማኖት፣ ስየ አብርሃ፣ ክንፈ ገብረመድህን፣ አርከበ እቁባይ፣ ገብሩ አስራት፣ ዓረጋሽ አዳነ፣ አውአሎም ወልዱ ወዘተ. ነበሩ።
    የተግባሩ አፈጻጸም በስየ አብርሃና በክንፈ ገ/መድህን ትእዛዝና አመራር ነበር። ገዳዮቹ፣ ብስራት አማረ፣ ሃሰን ሽፋ፣ ወልደሥላሴ፣ ዘአማኑኤል ለገሰ (ወዲ ሻምበል)፣ ተስፋዬ ጡሩራ (መርሳ)፣ ተስፋዬ አፈርሰው (አጽብሃ) ወዘተ. ነበሩ። ከ200 በላይ የሃለዋ ወያነ (06) ታጋዮችን በማሰለፍ ታጋዩን ገደሉት። የሃውዜን ጥቃትም በደርግ ሚግ 21-23-27 በእጅ አዙር ያስደበድቡት እነ ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ ወዘተ. ከዚህ ተነስተው ነው።
    ስየ አብርሃ ይህንን ክህደትና አረመኔያዊ ተግባር ከመፈጸሙ ትንሽ ቀደም ብሎ ከነመለስ፣ ስብሃትና አባይ ፀሃየ ጋር ተነስቶ የነበረው አለመግባባት ተጧጡፎ ቀጠለ። ስየ አብርሃ ሁሉንም ያጣ ብቻውን ሆኖ እየተናገረ መሄድ ጀመረ። ታጋዩ ሁሉ ጠላው፣ ራቀው። የፖሊት ቢሮ አባላት በየወሩ በስብሃት ነጋ የተፈቀደውን የኪስ ገንዘብ ብር 1,000 አልቀበልም አለ። ተወልደ፣ ገብሩ አስራትም እንደዚሁ አንቀበልም ብለዋል። ስየ አብርሃ በፈጸመው ክህደት እስከ ዛሬ በህወሓት ታጋይ እየተወገዘ ነው።
    3.  የህወሓት ለሶስተኛ ጊዜ መሰንጠቅ
    ወቅቱ ጥቅምት 1980 ነበር። የህወሓት ማ/ኮሚቴን ጨምሮ የማለሊት ማ/ኮሚቴ በአንድነት የተጠራ ስብሰባ ነበር። በዚህ ጊዜ የተነሱት ጥያቄዎች የስልጣን ሽኩቻ ሳይሆን የህወሓት-ማለሊት ፖሊት ቢሮ ዱሮ ከነበረውና ከተፈጸሙት ስህተቶች ያልተማረ፣ ብዙ ስህተት እየፈጸመ ነው። ከዚህ ስህተቱ መማር አለበት ወዘተ. በማለት የቀረበው ጥያቄ አነታራኪ ሆኖ በመቀመጡ፣ ስብሃት ነጋ በሚመራው ስብሰባ የቀረቡትን ጥያቄዎች በሙሉ ውድቅ አደረጋቸው። መለስ ዜናዊም የስብሃት ነጋን ሃሳብ ደገፈ። ጥያቄቆቹን ያነሱት በ1975 በ2ኛው ጉባኤ የተመረጡት የህወሓት አመራር ናቸው። እነሱም፤
    1. ክብሮም ገ/ማርያም የህወሓት ማ/ኮሚቴና የሰራዊቱ የሎጂስቲክ ዋና ሃላፊ የነበረ፣
    2. ኃ/ሥላሴ መስፍን፣ የህወሓት ማ/ኮሚቴ፣ ጠቅላላ የህወሓት ክፍለ ጦሮች የኮሚሳሮች የበላይ ሃላፊና ተቆጣጣሪ የነበረ፣
    3. ሰአረ ገብረጻድቅ፣ የህወሓት ማ/ኮሚቴና ጠቅላላ የህወሓት ማ/ኮሚቴና ፖሊት ቢሮ ጽ/ቤት ሃላፊ የነበረ፣
    4. ተክሉ ሃዋዝ፣ የህወሓት ማ/ኮሚቴና የቀድሞ የድርጅቱ ዋና የደህንነት ሃላፊ የነበረ ናቸው።
    ከላይ የተጠቀሱት አራቱ አመራር ባቀረቡት ሃሳብ አፈንጋጩ የእነ ግደይ ዘርአጽዮን እና አረጋዊ በርሄ ደጋፊዎች ተብለው ተወነጀሉ። ወንጃዮቹ፣ መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ፣ አባይ ፀሃየ፣ ሥዩም መስፍን፣ ገብሩ አስራት፣ አርከበ እቁባይ ናቸው፡ እነዚህ የፖሊት ቢሮ አባላት ተሰብሰበው ተወንጃዮቹን በማስጠራት እርማት እንዲያደርጉ ወሰኑ። በቀረቡበት ጊዜም፣ ያቀረባችሁት ሃሳብ ጸረ-ህወሓት-ማለሊት በመሆኑ፤ ከአመራርና ከሃላፊነታችሁ ተወግዳችሁ በተራ ታጋይነት ቀጥሉ ተብለው በስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ተሰናበቱ። ይህ ወቅት ህወሓት ለሶስተኛ ጊዜ የተሰነጠቀበት ወቅት ነበር።
    5.  የህወሓት ለአራተኛ ጊዜ መሰንጠቅ
    ይህ የህዋሓት ለአራተኛ ጊዜ መሰንጠቅ በ1993 የተፈጠረው ነው። ዋናው ዓላማ የስልጣን ሽኩቻ ነበር። ሌላው አንዱ ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ ሆኖ ሌላው ደግሞ ጸረ-ኢትዮጵያ ሆኖ የተፈጠረ መበታተን አይደለም። በእነ ስየ አብርሃ የሚመራው ቡድንም ጸረ-ኢትዮጵያና ጸረ-ሕዝብ ነው። ሃገራችን ኢትዮጵያን ያፈረሱ፣ የቀይ ባህር የባህር በሯን የሸጡና ያስነጠቁ፣ የዘር ማጥፋት እልቂት የፈጸሙ፣ ሕዝብን ለድህነት፣ ለችግር፣ ለበሽታና ለስደት የዳረጉ እነ መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስየ አብርሃ፣ ተወልደ ወ/ማርያም፣ ገብሩ አስራት ወዘተ. ተባብረው በሕዝብና በሃገር ከባድ ወንጀል የፈጸሙ ናቸው። በሁለት የተሰነጠቁበት ቀንደኛ ምክንያት ደግሞ የስልጣን ሽኩቻ ነው። ሌላ ምንም ነገር አልነበረም።
    6.  የህወሓት ለአምስተኛ ጊዜ መሰንጠቅ
    ህወሓት ኢትዮጵያን ወሮ በቅኝ ግዛት ከተቆጣጠረ በኋላ መሪው መለስ ዜናዊና የህወሓት አመራር ሁሉም በሃገራችን ከፍተኛውን የሥልጣን ወንበር ላይ ተደላድለው በመቀመጥ ኢትዮጵያን ለ21 ዓመታት በገዙበት ጊዜ በሕዝብና በሃገር ከፍተኛ ወንጀል በመፈጸም የኢትዮጵያን ሃብት ዘርፈዋል። ሕዝብን ያደኸየውን ስርዓት የመሰረተው መለስ ዜናዊ ሰኔ 7 ቀን 2004 ከዚህ ዓለም በሞት ተቀጠፈ። ብስራት አብሳሪው የኢትዮጵያ ሕዝብ መከታና መመኪያ እንዲሁም ዓይን እና ጆሮ ኢሳት በጥዋቱ የመለስ ዜናዊን ሞት ነገረን። ለወዳጆቹ ሃዘን ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የእፎይታ ቀን ሆነ። አረመኔው መሪ መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት ተቀጥፎ መኖሪያውን ሲኦል አደረገ። በዚህም ምክያት ህወሓት ለአምስተኛ ጊዜ ተሰነጠቀ። ከላይ እስከ ታች በቅራኔና በሥልጣን ሽኩቻ እንደ ዱባ ተፍረከረከ።
      1. የተህሓት ወግ አጥባቂ
    ተረካቢ (Old guard)
      2. ተንኳሽ
    (Catalyst)
      3. የመለስ ዜናዊ ውርስ
    (Legacy)
    ስብሃት ነጋደብረጽዮን ገ/ሚካኤልአባይ ወልዱ
    ብርሃነ ገ/ክርስቶስጌታቸው አሰፋ
    ቴዎድሮስ አድሃኖምበየነ ምክሩ
    ጸጋይ በርሄአለም ገ/ዋህድቴዎድሮስ ሃጎስ
    አባዲ ዘሞክንደያ ገ/ሕይወት
    ብርሃነ ማረት፤
    ትርፉ ኪ/ማርያም
    እነ ስብሃት ነጋ ያላቸው ደጋፊ ጥቂት ሲሆን፤ እነ አባይ ወልዱ የህወሓት ማ/ኮሚቴውን በብዛት ይዘዋል። እነ ደብረጽዮንም ከነአባይ ወልዱ ድጋፍ አላቸው። አንድ ተረት አለ፣ ‘ከዝንጀሮ ቆንጆ ምን ይመራርጡ’ እንደሚባለው ነው። የህወሓት መንጋ ከአመራሩ ጀምሮ እስከ ተራ አባላቱ በወንጀልና በሰው ልጅ ደም የታጠበ ነው። በዚህ ዓይነት በሳሞራ የኑስ የሚመራው ሰራዊት፣ ፖሊስ፣ ደህንነቱ፣ የፌደራሉ ሁሉ ወንጀለኞችና ጸረ-ሕዝብ ናቸው። መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበረበት ጊዜ በ1993 የተነሳው የስልጣን ሽኩቻ በሁለት ሲሰነጥቀው፤ አሁንም ተመሳሳይ ዓይነት እጣ የደረሰው ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ ነው፤፡ ህወሓትን በሶስት የከፈለው ዋናው የሥስልጣን ሽኩቻ ብቻ ሳይሆን ኢፈርትን ማን ይምራ፣ ማንስ ይቆጣጠር የሚለው ነበር። በ’ለ’ ስር የተዘረዘሩት የኢፈርት ዋናው የዝርፊያ መሳሪያ ስለሆነ በኛ ይመራ ባዮች ናቸው። በ’ሀ’ ምደብ ስር ያሉት እነ ስብሃት ነጋ ከላይ እሰክ ታች ኢፈርትን መቆጣጠርና መምራት ያለብን እኛ ነን ብለው ቁመዋል። በተጨማሪም፣ ከሥልጣኑም የሚንስትርነት ቦታ ለኛም ይገባናል ባዮች ናቸው። በተለይ አዜብ መስፍን በሕገወጥ መንገድ ከስብሃት ነጋ የወሰደችው የኢፈርት መሪነት ለኛ tedrosይመለስልን ሲሉ በ’ለ’ እና በ’ሐ’ የተሰለፉት አልተቀበሉትም። አዜብ መስፍንን ከኢፈርት አስወግደን በሌላ ሰው እንተካታለን በማለት ተስማምተው ብርሃነ ኪዳነማርያምን በቦታዋ በዳይሬክተርነት አስቀመጡት። እነ ስብሃት ነጋ ግን ይህንን አልተቀበሉትም። የኢፈርት የበላይ ሃላፊ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ነው። እነ ስብሃት ነጋ በዚህ ግራ ተጋብተዋል።
    በ’ለ’ ምደብ ያሉትን እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ትልቁ ጥረታቸው በአባይ ወልዱ የሚመራው በ’ሐ’ ምድብ ስር ያሉት በ’ሀ’ እና በ’ሐ’ ምድብ ያሉት እንዳይስማሙና በመካከላቸው ሆነው ነገር በመተንኮስ ቅራኔ ውስጥ እንዲገቡ ያደርጋሉ። አዜብ መስፍንን ካነሳን ዘንድ፤ አንበሳ ባንክን ወዘተ. ተቆጣጠሩ ተብሎ ለነስብሃት ነጋ የተሰጠ ገጸ በረከት ነው። የኤርትራው ተወላጅ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ‘ኢትዮ ቴሌኮምን’ የግል ሃብቱ በማድረግ የሃገርና የሕዝብ ሃብት እየበዘበዘ ገንዘቡን በቻይና ባንክ በማስቀመጥ ኢትዮጵያን እያደማ ይገኛል። በ2007 ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን ፍላጎትም አለው።
    ኤርትራዊው ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ የሃገር ሃብት እየዘረፈ በማሌዢያና በተለያዩ ሃገራት ባንኮች ሃብቱን እያደለበ የሚገኝ የህወሓት መሪ ነው። ኢፈርትንም መለስ ዜናዊ ከሞተ በኋላ በሃላፊነት የተረከበ ሰው ነው። በ2007 ምርጫም በእነ ወልዱ ድጋፍ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ ያገኘ ሰው ነው። እነ አባይ ወልዱ በትግራይ ውስጥ የሚገኙት የኢፈርት ፋብሪካዎች፣ እንደ አልመዳ ጨርቃ ጨርቅ፣ መሶብ ሲሚንቶ ፋብሪካ፣ መስፍን ኢንጂነሪንግ ወዘተ. ወፍራሙን ድርሻ ያገኛሉ። በዚሁ መሰረት ኢፈርት ከተመሰረተ ከ1985 ጀምሮ ለመንግሥት ግብር አይከፍልም። ከብሄራዊ ባንክና ከንግድ ባንክ የሚበደረውን ገንዘብ አይመልስም፣ እንዲያስከፍለው የሚያስገድደው ሕግም የለም። የተለያዩ እቃዎች ሲያስገባና ሲያስወጣ ቀረጥ ለመንግሥት አይከፍልም። ምክንያቱም ኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ስር የያዘው የህወሓት ባለሥልጣናት የግል ንብረታችው ስለሆነ በማንም ሕግ የማይገዛ ኢፈርት ነው።debretsion gebremichael
    መለስ ዜናዊ ከሞተ በኋላ በህወሓት ውስጥ ከፍተኛ ውዝግብ ተፈጥሯል፣ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ሃይላቸውም የተበታነ እርስ በርሳቸው አለመተማመን ነግሷል። ሁሉም የህወሓት አመራርና አባሎቹ ደጋፊዎቹ በሙስና የተጨማለቁ በዘር ማጥፋት ወንጀል በመሰማራት ከ8.9 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ የገደሉ ናቸው። ከ30 ሚሊዮን በላይም ኢትዮጵያዊ ከተወለደበት ከሚወዳት ሃገሩ ሠርቶ ከሚበላባት፣ ልጆቹን አስተምሮ፣ አሳድጎ ለቁም ነገር ካበቃበት መሬቱ በማፈናቀል ግማሹ ለስደት ግማሹ ለሞት፣ ግማሹ ለችግር፣ ለረሃብ፣ መኖሪያ አልባ አድርገውታል። ከዚህ በመነሳት ህወሓቶች በጽኑ አቋም የሚስማሙበት አጀንዳ አላቸው። ። ከህወሓት የተባባሩ አመራር የነበሩትም በዚህ በጸና አቋም ይስማማሉ።
    1. አሁን በኢትዮጵያ ያለው ሕገመንግሥት የህወሓት ሕገመንግሥት ነው። ይህም ከ1967 እየታገልን ይዘነው የመጣን የሕይወታችን እና የንብረታችን መድን ነው። ይህ ሕገመንግሥት ከተናደ አሁን ያለነው የተባረሩት አመራርም ተለቅመን ታሰርን፣ ሃብታችን ተወረሶ እኛም እንገደላለን። ስለሆነም ያለውን ሕግመንግሥት መክላከል የግድ ይሆናል። ሁሉም በዚህ ይስማማሉ፣
    2. ኢፈርት የህወሓት ሃብት ነው። ኢፈርትም በኢትዮጵያ ያሉትን ገዢ ተቋማት በተዘዋዋሪና በቀጥታ የሚቆጣጠር ነው። ለምሳሌ፣ ኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ብሄራዊ ባንክ፣ ንግድ ባንክ፣ መአድናት፣ ትራንስፖርት ወዘተ. የሃገሪቱ ንግድም ከትንሹ እስከ ትልቁ የሚቆጣጠር ነው። ይህ የደም ስራችን ከወደመ በሕዝብ ቁጥጥር ከዋለ ህወሓትና መሪዎቹ ብቻ ሳይሆኑ የህወሓት መንግሥታዊ ተቋማት ጭምር ይወድማሉ። ስለሆነም ባለን አቅማችን ኢፈርትን መከላከል በበለጠ ማሳደግ አለብን። በዚህም በማያወላውል መንገድ ይስማማሉ፣
    3. የሕዝብ የአመጽ ተቃውሞ ወይም አብዮት ከተነሳ ባለን መከላከያ ሰራዊት ደህንነት፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻ፣ ልንመልሰው አንችልም። ሕዝቡ ከአሸነፈ የህወሓት አመራር አባሎችና ደጋፊዎቻችንን በእሳት እንደሚቀቅለን እናውቃለን። ለዚህ መድሃኒቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ በየጎሳ ከፋፍለን አሁን ባለው አይነት ደፍጥጠን ማጥቃት፣ ተቋዋሚ ድርጅቶችን ማዳከም፣ መግደል ማዋከብ አለብን። የአገዛዛችን መንገድ ሕዝቡን ማስጨነቅ፣ ረሃብ፣ በሽታ፣ በስደት እንዲጓዙ ማድረግ እነዚህን በዋናነት እንደ መሳሪያ መጠቀም አለብን። ወጣቱን ዜጋ ደግሞ በሽርሙጥና፣ ሃሺሽ ወዘተ. በብዛት አስፋፍቶ ከጥቅም ውጭ ማድረግ። በጎሳ ከፋፍለንም ኢትዮጵያዊነት የሚል ስር የሰደደውን እምነት ማጥፋት፣ የአማርኛ ቋንቋን ማጥፋት፣ በየትኛውም ጎሳ የሚገኘውን ስር መሰረቱን ነቅለን እንዳልነበረ ማድረግ። በዚህም ሁሉም ይስማማሉ።
    ኢትዮጵያን አሁን ማን እየመራት ነው?
    መለስ ዜናዊ ከሞተ በኋላ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስቴር ተብሎ እንደተሰየመ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያውቀዋል። ነገር ግን ኃ/ማርያም የእውነት ሳይሆን የውሸት ጠ/ሚኒስቴር ነው። ኢትዮጵያና ህዝቧ ላይ አሁንም መዋቅሩን የዘረጋው ህወሓት ነው። ከመጋረጃ ጀርባ ሆነው ኢትዮጵያን የሚመሩትና የሚያስተዳድሩት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል፣ ቴዎድሮስ አድሃኖምና ንዋይ ገብረአብ ናቸው። ስለዚህ ኢትዮጵያን ማን እየመራት ነው ለሚለው ጥያቄ በትክክል ከላይ የተጠቀሱት ሶስቱ የህወሓት አመራር ናቸው። የስርዓቱን መዋቅርም በነዚህ ግለሰቦች ይመራል። ኃ/ማርያም ደሳለኝ አድርግ ያሉትን የሚያደርግ ጉልቻና ቃል አቀባይ ነው።
    በ1922 የተወለደው የ83 ዓመቱ ዘራፊና ገዳዩ ሽማግሌ ስብሃት ነጋ የሚመራው ቡድን ለባለሥልጣናቱ እንቅፋት አይሆንባቸውም። መሪዎቹ የሚፈልጉት ዝርፊያ ብቻ ነው። እነ አባይ ወልዱ ከነ ደብረጽዮን ጋር ተስማምተው በትግራይ ሪፓብሊክ መንግሥት ውስጥ እጃችሁን አታስገቡ። ገንዘብ እንፈልጋለን፣ ከፍተኛ ባጀት መድቡልን፣ እኛም የእናንተ ደጋፊዎች ነን በማለት ተስማምተዋል።
    hailemariam speakingለሚቀጥለው የ2007 ምርጫ ህወሓት በአሸናፊነት ወጥቶ ለጠ/ሚኒስቴር፣ ም/ጠቅላይ ሚኒስቴር የሚሆኑትን እጩዎቹን አዘጋጅቷል። ጠቅላይ ሚኒስቴር ይሆናል ተብሎ የታጨው ቴዎድሮስ አድሃኖም ሲሆን፣ ም/ጠቅላይ ሚኒስቴር ሊሆን የታሰበው ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ነው። “አባይ ማደርያ የለው ግንድ ይዞ ይዞራል” ማለት ይህ ነው። ህወሓት የተዳከመ፣ የበሰበሰ ግንድ ነው። በዚህ ደረጃ ላይ ያለ ፋሽስታዊ ድርጅት ኢትዮጵያን ረግጦ የመግዛት አቅም የለውም። በኢትዮጵያ ሕዝብ ሃይል ክንድና አንድነት ይደመሰሳል። ይህንን ድክመታቸውን በመጠቀም ሃገር ቤትም በውጭ ሃገር የምንገኘውን ጨምሮ አንድነታችንን አጠናክረን በሕዝባዊ አመጽ ወያኔ ህወሓትን የመደምሰስ ጊዜው አሁን ነው።
    የመለስ ዜናዊ ራእይ
    በዚሁ ጥቂት ጥያቄዎችን በመለስ እደመድማለሁ። መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ ማን ነው?
    መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ የጠላት ጠላት ደመኛ ጠላት ነው። ከአባቱ፣ ከእናቱና ከአያቶቹ የወረሰው በኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ የፈጸመው ግፍ፤ የሃገር ማፍረስ ድርጊት በታሪክ የማይረሳ ነው። እሱ ብቻ ሳይሆን የህወሓት አመራርንም ይጨምራል። የስም ዝርዝራቸውን በተለያዩት ጽሁፎቼና ከዚህ በላይም ስላካተትኳቸው እንሱን መመልከትና ማመሳከር ይቻላል።
    የመለስ ዜናዊ ራእይ በኢትዮጵያ ልማት፣ እድገት፣ ዲሞክራሲ ማለትስ ምን ማለት ነው? በእርሱ አመራር ለ21 ዓመታት ኢትዮጵያ በልማትና በዲሞክራሲ አብባለች የሚሉት የህወሓት ደጋፊዎችና አጋር ድርጅት ተብለው የሚጠሩት ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ኢትዮጵያ ስብስብ ብቻ ናቸው። ብዙ ለሆዳቸው ያደሩም አሉባቸው። ነገሩ የተጋላቢጦሽ ነው። መለስ ዜናዊ የሚመራው ህወሓትና አመራሩ በተፈጥሮው ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ዲሞክራሲ ነው። ህወሓት አፈጣጠሩ አምባገነን እና ፋሽስት፣ እንዲሁም ጸረ-ዲሞክራሲ ሆኖ ያደገ ከመቅጽበት የልማት፣ እድገትና ዲሞክራሲ አራማጅ ሊሆን አይችልም። ጎባጣና ጠማማ ሆኖ ያደገ ባህር ዛፍ ተቃንቶ ለኤሌክትሪክ ምሰሶ ወይም ለቤት መስሪያ ማገር ልታደርገው አትችለም። በምሳር ቆራርጦ ማገዶ ከማድረግ ውጪ። ህወሓትን በዚህ አይነት ልንመለከተው ይገባል። ስለሆነም የመለስ ዜናዊ ራእይ ጸረ-ሕዝብ፣ ጸረ-ልማት፣ ጸረ-እድገት፣ ጸረ-ዲሞክራሲ ነው። መለስና ግብረአበሮቹ በዘር ማጥፋት ወንጀል የተሰማሩ፣ በሙስና የሕዝብና የሃገር ሃብት የዘረፉ፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ በፋሽስት መዋቅራቸው ያሰቃዩና የገደሉ ናቸው። እንደዚህ ያለ ጨቋኝና ፋሽስት መንግስት ልማታዊ ሊሆን አይችልም።
    መለስ ዜናዊና ህወሓት ለኢትዮጵያና ሕዝቧ ምን ናቸው? በመለስ ዜናዊና በስብሃት ነጋ የሚመራው ፋሽስት ፓርቲ፣ ኢትዮጵያን ከግንቦት ወር 1983 ጀምሮ ከተቆጣጠሩ ወዲህ ኢትዮጵያና ሕዝቧ በወያኔ ሀውሓት ቅኝ አገዛዝ የወደቀችበት ወቅት ሆኖ፣ እነሆ ቅኝ ገዢው ህወሓት በሃገራችን አረመኔያዊ ድርጊት እየፈጸመ ይገኛል። በመለስ ዜናዊ የአገዛዝ ዘመን የኢትዮጵያ ሉአላዊንት ፈርሷል። ጥንታዊና ታሪካዊ የቀይ ባሕር ወደቦቿን አጥታለች። ሕዝብ በዘሩ እየታየ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል። ስለዚህ መለስ ዜናዊና ህወሓት እንዲሁም አመራሩ የኢትዮጵያ ደመኛ ጠላት ናቸው።
    መለስ ዜናዊ የወታደራዊ ሳይንስና ስትራተጂ ባለ ራእይ ይባላል። ይህ አነጋገር ደረቅ ውሸት ነው። መለስ ዜናዊን የሚያውቁና አብረውት በትግሉ የነበሩ ታጋዮች የማይቀበሉት ጉዳይ ነው። የህወሓት መንጋ በምን ዓይነት የውሸት አዘቅት ውስጥ እንደሰመጠ በግልጽ የሚያሳይ ነው። መለስ ዜናዊ ከትግሉ መጀመሪያ አንስቶ ለብዙ ዓመታት አብረን ተጉዘናል። በጣም የሚተማመንብን ጓደኞቹ ተክሉ ሃዋዝና እኔ ገ/መድህን አርአያ ነበርን። በሚገባ ስለምናውቀው የወታደራዊ ስታርቴጂስት አልነበረም። እውቀቱም ችሎታውም ፈጽሞ አልነበረውም። ሃቁ ይህ ነው።
    “ጅብ በማያውቁት ሃገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ” እንዳለው ዓይነት ነው። መለስ ዜናዊ ከፈሪነቱ የተነሳ በተለያዩ ጦርነቶች ፈርቶ የሸሸ፣ በህወሓት ታሪክ ውስጥ በፈሪነቱ ቀዳሚውን ስፍራ የያዘ ግለሰብ ነው። ከሸሸባቸው ጦርነቶች ለአብነት፤
    1. በ1969 ከአድዋ ኦፐሬሽን ጦርነቱ እንደተጀመረ ፈርቶ የሸሸ፣
    2. በ1970 ከአዲ ደእሮ ፈርቶ የሸሸ፣
    3. በ1971 መጀመሪያ ላይ ከማይቅነጠል ውጊያ ፈርቶ የሸሸ፣
    4. በ1971 ህዳር ወር ከፈረስ ማይ ጦርነት ፈርቶ የሸሸ፣
    5. ሰኔ ወር 1971 ከሃገረ-ሰላም ውጊያ ታመምኩ ብሎ መሬት ላይ ሲንከባለል በበቅሎ ተጭኖ እንዲምለስ የተደረገው  ናቸው። በምስክርነት የሰራዊቱ የጦር አዛዥ አረጋዊ በርሄ የሚያውቀው ጉዳይ ነው።
    በህወሓት ውስጥ ማንም ታጋይና አመራር የሚያውቀው ሃቅ አለ። ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ የነደፈው ጥናት እያደረገ ወታደረአዊ ስትራተጂ ወታደራዊ ታክቲክ የአሸዋ ገባታ ለረጅም አመታት ጥናት በማካሄድ የጻፈና ያዘጋጀ ብቸኛው አረጋዊ በርሄ ነው። ለሁሉም ወታደራዊ አመራር ስየ አብርሃ፣ ሃየሎም አርአያ ወዘተ. አስተምሮ ያሳደጋቸው አረጋዊ በርሄ ነው። ስየ አብርሃ ይሁን ሌላው የሚኩራሩበት ውሸት ነው። ወያኔ ህወሓት እስከ አሁን የሚጠቀሙበት ወታደራዊ ጉዞ በአረጋዊ በርሄ የተዘጋጀ እንጂ መለስ ዜናዊ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ወታደራዊ ሳይንስ ይሁን ስትራተጂ የጤፍ ቅንጣት የምታክል እውቀት አልነበረውም። ሁሉም የሚዋሸው ለሆዱ፣ ለጥቅሙና የሙስና ዘርፊያውን በስፋት ለመቀጠል ስለሚፈልግ የሚመታው የውሸት ነጋሪት ነው።
    ግደይ ዘርአጽዮን ከህወሓት ወጥቶ ወደ ስደት ሲሄድ በህቡር ገብረኪዳን መሪነት ተክለወይን አሰፋ፣ ተሻለ ደብረጽዮንን ጨምሮ ተፈትሾ የያዘውን ሰነዶች ሁሉ፣ ብጣሽ ወረቀት ሳትቀር፣ ጠራርገው በመውሰድ ባዶ እጁን ሱዳን ገባ።
    አረጋዊ በርሄ፣ ህቡር ገ/ኪዳን፣ ስብሃት ነጋ፣ አርከበ እቁባይ ሁነው ለብዙ ዓመታት ሲያካሂዱት የነበረውን ወታደራዊ ጥናትና ስትራተጂ የአሸዋ ገበታ፤ በትልልቅ ወረቀቶች ላይ በሰእል መልክ የተዘጋጁ ጠቅላላ ወታደራዊ መጻሕፍት ብጣሽ ወረቀት ሳትቀር በሁለት የማዳበሪያ ከረጢት ሞልተው የወረሱትን በታጋዮች አሸክመው ለመለስ ዜናዊ አስረከቡት። ‘በሰው ደንደስ በርበሬ ተወደሰ’ እንደተባለው፣ መለስ ዜናዊ ባልሰራውና በማያውቀው ወታደራዊ ስትራተጂ የአሸዋ ገበታ ንድፈ ሃሳብና አረጋዊ በርሄ ደክሞ ያዘጋጀው ነው። አሁን ወያኔ የሚጠቀምበት ወታደራዊ አካሄድ የአረጋዊ በርሄ ሥራና ጥናት ነው። ባልሰራኸው፣ በማታውቀው ጥበብ የራስህ አስመስለህ መጠቀም ያስንቃል፣ ያዋርዳል። ስለዚህ መለስና የህወሓት መንጋ ውሸታምና በምን ዓይነት ድቅድቅ የውሸት ጨለማ እንደተዘፈቁና ማንነታቸውን እንዲያውቁ ይህንን የጽሑፍ ሰነድ ያንብቡ።
    የስብሃት ነጋ መርዶ ነጋሪ
    ቀደም ብሎ በተህሓት-ህወሓት የነበረው የኢትዮጵያውያን አመራር ነበር። እነ አቶ ገሰሰው አየለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሴ (መሃሪ) ተክሌ፣ አጽብሃ ዳኘው፣ ዶ/ር አታክልት ቀጸላ በምን ምክንያት በምን ዘዴ እንደገደሏቸው በትክክል አስቀምጬዋለሁ። በየካቲት 1981 በወቅቱ የኢትዮጵያ መንግሥት የነበረው ደርግ ትግራይን ለቆ መውጣቱን ተከትሎ ወያኔ ህወሓት ካለምንም ውጊያና ውጣ ውረድ ትግራይን ተቆጣጠረ። ሃቁ ይህ ሆኖ፣ በ1983 በለስ ቀንቷቸው አዲስ አበባ ዘው ብለው ኢትዮጵያን እነደተቆጣጠሩ፣ ነብሰ ገዳዩ ስብሃት ነጋ በመርዶ ነጋሪነት ተሰማራ። የዶ/ር አታክልት ቀጸላ ወላጅ አባት የሚኖርበት ቤት በመሄድና እራሱን በማስተዋወቅ የዶ/ር አታክልትን ሞት ነገራቸው። በአረጋዊ በርሄ እንደተገደለ ሲነግራቸው፣ አረጋዊ በርሄ የማን ልጅ ነው ብለው ሲጠይቁት፣ የቀኛዝማች በርሄ ገብረማርያም ነው ሲላቸው፣ የልጅ በዛብህ ፍላቴ ልጅ? ብለው ጠየቁት፣ አዎን አላቸው። የቅርብ ወንድሙ ለምን ገደለው? ሲሉት፣ በአረጋዊ መገደሉን እንጂ ሌላውን ሳይነግራቸው መርዶውን አሰምቶ ተሰናበተ። በጅሮንድ ቀጸላም በሚወዱት ልጃቸው መርዶ የተነሳ ታመው ከብዙ ስቃይ በኋላ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
    ስብሃት ነጋ ይህ አልበቃውም። አድዋ አቶ ዳኘው ገ/ሥላሴ ቤት ደረስ በመሄድ የአጽብሃ ዳኘው ወላጅ እናትና ጠቅላላ ቤተሰቡ ባሉበት፣ በአክብሮት ተቀብለው ቤት ያፈራውን ከጋበዙት በኋላ፣ እናቱ ወ/ሮ ማና ተፈሪ ልጄ ‘ሞላ’ (የቤት ስሙ) እንባቸውን እያፈሰሱ፣ ልጄ ጠፋብኝ፣ የምታውቀው ነገር አለ ወይ ብለው ሲጠይቁት፣ ስብሃት፣ አጽብሃ፣ ሰዊት ተገድሎ ከሞተ ብዙ ዓመት ሆኖታል አላቸው። አባትየው ቀበል አድርገው እንዴት ሞተ ሲሉት፣ አረጋዊ በርሄ ገደለው አላቸው። አረጋዊ፣ የቀ/አ በርሄ ገ/ማርያም ልጅ? ብለው ሲጠይቁት፣ አዎን አላቸው። ያሳደገው ወንድሙ ገደለው? የአጽብሃ ዳኘው እናት በዚህ ደንግጠው ታመው በሃዘን በሽታ ተሰቃይተው ሞቱ። ሽማግሌው አቶ ዳኘው ገ/ሥላሴ አሁንም በሕይወት አሉ። የዶ/ር አታክለት ቀጸላ ወላጅ አባትም በመርዶው ምክንያት ታመው፣ ራስ ወርቅ ልጄ እንዳሉ ሞቱ። በ1998 የሁለቱ ቤተውስቦች ስልክ በቀጥታ ወደ እኔ ደውለውልኝ ተነጋግረናል። በዚህ ሃሳብ ላይ እንዳለን፣ የዶ/ር አታክልት ቀጸላ ወላጅ አባት በጅሮንድ ቀጸላ ብሩ፣ ወላጅ እናቱና የእኔ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ገ/መድህን አርአያ ወላጅ እናቴ ወ/ሮ አጸደ ገብሩ እናት፣ የሁለቱ እናቶች ታላቅና ታናሽ የአንድ አባትና እናት ልጆች ናቸው። በዚህ መሰረት ነው የዶ/ር አታክለት ቀጸላ ቤተሰቦች አረጋዊ በርሄ በምን ምክንያት እንደገደለው የጠየቁኝ። እኔም ስብሃት (ወ/ሥላሴ) ነጋ የነገራችሁ ውሸት ነው። ዶ/ር አታክልትን የገደለው ስብሃት ነጋ ነው፣ በማለት በጽሑፍ እንደገለጽኩት ስነግራቸው አምነውኝ ተለያያን። ያመኑኝ ምክንያት የአታክልት መገደል ለእኔም የሚሰማኝ ልክ እንደ እነሱ ስለሆን ነው። ለእኔም ለነሱም ወንድማችን ነው።
    ቀጥሎ ከትንሽ ወራት በኋላ በ1998 ከአጽብሃ ዳኘው ቤተሰብ ወንድሙ ከእንግሊዝ ሃገር ደወለልኝ። በጽሑፍ እንዳስቀመጥኩት ገልጬለት አልቅሶና አጽናንቼው ተለያየን። ቀጥሎ ለሁለተኛ ጊዜ በ2000 ወንድሙ ደውሎልኝ፣ ያቀረብኩለትን ሁሉ እንዳለ አምኖ ተቀበለኝ። ሌላው ያቀረበልኝ ጥያቄ ቤተሰቦቼ በአረጋዊ በርሄ ቅሬታ አድሮባቸው ነበር፤ በምን አይነት ይቅርታ ልጠይቀው፣ እባክህ ንገርልኝ ሲለኝ፣ የለም ከሆነ ባንተ ነው መሆን ያለበት ብዬው እንደሚደውልለት ነግሮኝ ተሰነባበትን። አረጋዊ በርሄ ግምት ያልሰጠው እውነት አለ። የህወሓት ፕሮግራምን ጽፎ ለ12 ዓመት በከፍተኛ አመራር ላይ ሆኖ ያስተዳደረው ድርጅት ነው። ማንም የማያቀውን የድርጅቱን ወንጀሎች በዝርዝር ያውቃል። ህወሓት በሥልጣን ላይ ሆኖ ለፈጸመው ግፍ ተጠያቂ እንዳይሆን አረጋዊ በርሄ አጋጣሚውን ተጠቅሞ ወያኔን ማጋለጥ አለበት።
    እነ ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ ወዘተ. በትግሉ ጊዜ የተገደሉት ታጋዮች፣ ሰላማዊ ዜጎች በስንት ሺህ የሚቆጠሩ ናቸው። ከ1982 በዘመቻ መልክ ተነስተው ያስፈጁትን አረጋዊ በርሄ እንደገደላቸው አድርገው ስሙን በክፉ መልክ አጥፍተውታል፣ አሁንም እንደቀጠሉበት ነው። የህወሓት አባላትና ደጋፊዎቹ እስከ አሁን እኛን የፈጀን አረጋዊ በርሄ ነው እያሉ ይገኛሉ። እሱም ይህንን ነገር በትክክል ያውቃል። አረጋዊ የሚለውና የሚሟገተው፣ ማስረጃችሁን አቅርቡ እያለ ነው። ይህ አባብሉ ግን ትክክል አይደለም። የፖሊት ቢሮ አባልት ሁሉ በየ06 ሃለዋ ወያነ እየተበተኑ ሕዝብ የጨረሱት አመራሩ ናቸው። በ06 ሃለዋ ወያነ ሃላፊዎች የምርመራ ሪፖርት ጭፍን ፍርድ ሲሰጥ የነበረው አመራር ነው። በሰነድ ተደግፎ የሚፈጸም ግደሏቸው የሚል ትእዛዝ በተህሓት-ህወሓት አሰራር አይታወቅም።
    እነ ስብሃት ነጋ በአረጋዊ በርሄ ላይ የሚያካሂዱት የስም ማጥፋት እልባት ማግኘት አለበት ከሚል ሃሳብ ተነስቼ መጋቢት 2 ቀን 2000 በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የትግራይ ተወላጆች ማህበር፣ በዶ/ር ግደይ አሰፋ ሊቀመንበርነት፣ በአቶ ተስፋየ አጽብሃ የሚመራው ቡድን በተጠቀሰው ቀን ተሰበሰበ። ለአረጋዊ በርሄ ያቀረብኩት ሃሳብ በእነ ስብሃት ነጋና በወያኔ ስርዓት ስምህ እየጠፋ ነው። አንተም በመጀመሪያ ማድረግ ያለብህ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ጠይቀህ በህወሓት የተፈጸሙትን ወንጀሎች ለሕዝብ አቅርብ። ያን ስታደርግ የአእምሮ እረፍት ታገኛለህ። በህወሓት በርካታና ከባድ ወንጀሎች ተፈጽመዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅር ባይ ነው የሚል ሃሳብ አቀረብኩለት። በወቅቱ የነበሩ አመራርና በቴሌ ኮንፈረንስ የነበሩት የሚመሰክሩት ጉዳይ ነው። አረጋዊ በርሄ ለምን ደፈርከኝ ብሎ ብዙ ተናገረ። ቁም ነገሩ ቴሌ ኮንፈረንስ በመሆኑ ነው እንጂ በአካል አጠገቡ ብገኝ ኖሮ ረጋግጦ ያጠፋኝ ነበር። የሁላችንም ግንኙነት ከዚህ ጊዜ በኋላ ተቋረጠ። ጥሩ ምክር በመለገሴ ጠላት አፈራሁ። የመከራና የችግር ጊዜ ወንድሙን ጠላኝ። ይባስ ብሎ የህወሓት ጠላትና ጽንፈኞች በማለት፣ አስገደ ገ/ሥላሴን እና እኔ ገ/መድህን አርአያን ፈረጀን። ይህን ለማለቱ ብዙ የሰው ምስክሮችት አሉን። የተማረ ሰው ነው። በህወሓት ውስጥ ያለፈ አመራር ሁሉ፣ ከትግሉ መጀመሪያ አንስቶ፣ ብዙ ወንጀል ፈጽሟል፣ በመፈጸም ላይም ነው። ስለዚህ ማንም አመራር እኔ ነፃ ነኝ የሚል ካለ ተሳስቷል። ልክ እንደ ግደይ ዘርአጽዮን ጥፋተኛ ነኝ ብሎ ደጋግሞ እንደሚናገረው ሌላውም ይህንን አርአያነት መከተል አለበት።
    ውድ ኢትዮጵያውያን የህወሓት ታሪክና እንወቀው የሚሉት ጽሑፎቼ በዝግጅት ላይ ናቸው። በጥቂት ወራት ውስጥ ለሕዝብ ይቀርባሉ የሚል ጽኑ እምነት አለኝ። ሶስተኛው ጽሑፌ ደግሞ “ተጠያዊዎቹ እነማን ናቸው” ይሚለውን በማዘጋጀት ላይ ነኝ። ከማገብት-ተሓህት-ህወሓት የመጡ አመራር አንድ በአንድ ምን ሰሩ፣ በምንስ ይጠየቃሉ የሚለው ሰፊና ግልጽ መጽሓፍ እየተዘጋጀ ነው።
    ማሳሰቢያ፡ በድህረ ገጽ የማስተላልፋቸውን ጽሁፎች ኢትዮጵያዊ ሁሉ በማተም ሰብስባችሁ “የህወሓት ገበና” በማለት በማህደር አጠራቅሙት። ጥሩ የሰነድ ማስረጃ ነው። የህወሓት አመራርና ካድሬዎቹ በሕዝብ የሚፈረዱበት ቀን ደርሷል።
    ገብረመድህን አርአያ
    ህወሓት በኢትዮጵያ ሕዝብ ሃይል ይደመሰሳል!!!
    አውስትራሊያ
    2006 ዓም የነጻነት ዓመት ናት!!!
    መስከረም 6 ቀን 2006