Friday, May 31, 2013

ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋሁን ቤንሻንጉል-ጉምዝ ውስጥ ታስሯል



ቤንሻንጉል-ጉምዝ

ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋሁን ቤንሻንጉል-ጉምዝ ውስጥ ታስሯል

“ኢትዮ-ምኅዳር” ለሚባለው ሣምንታዊ ጋዜጣ ከአማራ ክልል ሲዘግብ የቆየው ሙሉቀን ተስፋሁን በቤንሻንጉል-ጉምዝ ፖሊስ መያዙን የጋዜጣው ምንጮች አስታወቁ።
የቤንሻንጉል-ጉምዝ ወረዳዎች
ቤንሻንጉል-ጉምዝ

“ኢትዮ-ምኅዳር” ለሚባለው ሣምንታዊ ጋዜጣ ከአማራ ክልል ሲዘግብ የቆየው ሙሉቀን ተስፋሁን በቤንሻንጉል-ጉምዝ ፖሊስ መያዙን የጋዜጣው ምንጮች አስታወቁ።

ሃምሳም ሰውም ይውጣ ሃምሳ ሺህ ግን አንድ ፀባይ እሱም “ፍፁም ሰላማዊ!”

935293_421802944584325_731290226_nአቤት የርዕሴ ርዝመት… ደግሞ በዛ ላይ ቀጥሎ የምናገረውን ማሳበቁ! “ቢወዳት ነው ቢጠላት ባሏ በሻሽ አንቆ ገደላት” አይነት ሆነኮ፡፡
ለማንኛውም ቀጥሎ ስለ ሰላማዊ ሰልፉ ጥቂት ልናወጋ ነው፡፡ በአማርኛ፣ በኦሮምኛ፣ በትግርኛ እና በጥቅሉ በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ስለ ሰላማዊ ትግል ስናወራ ስለ ሙስሊም ኢትዮጵያውን በማውራት ብንጀምር የወጋችንን ደረጃ ከፍ ደርገዋል ሞገስም ይሰጠዋል እና  እንቀጥል…

Wednesday, May 29, 2013

“አባይ ይገደብ፤ ኢህአዴግም ይገደብ፤ አባይ ይቀየስ ኢህአዴግም ይቀየስ!”

bereket_simon“የዘመናት ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሰራዊት ከዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬድዮ ጣቢያ ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ተቆጣጥሮታል፡፡ ጉንቦት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህረት!” አለ ታጋዩ…
“የዘመናት ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሰራዊት ከዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬድዮ ጣቢያ አሁን ደግሞ ለራሱ ጥቅም ተቆጣጥሮታል፡፡ ቆጣጥሮታልም፤ ግንቦት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህረት!” አልኩ እኔ…
“ኢህአዴግ ደርግን ደመሰሰ እና ሌላ ቀዳበት”  አለ ልጅ ያሬድ!  ”ኢህአዴግ ደርግን ደምስሶ በደርግ ዜማ ሌላ ቀዳበት” አልኩ እኔ
ዛሬ ግንቦት ሃያ ነው፡፡

ማንዴላ በመጨረሻዋ የፍርድ ቀን ለዘረኞች ያለው

ኢትዮጵያን በቁጥጥሩ ስር ያዋላት የትግራይ ዱር አራዊት ቡድን ዛሬ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየጫነ ያለውን የአፓርታይድ አይነት ስራት እነ ኒልሰን ማንዴላ ከደቡብ አፍሪካ ምድር ከስሩ መንግለው ለመጣል እጅግ ብዙ መስዋእትነትና ምእተ አመት የሚጠጋ ጊዜ ነበር የወሰደባቸው።Former South African president Nelson Mandela
የደቡብ አፍሪካውን የጥቂት ነጮች አፓርታይ መንግስት ለማስወገድ ኤ ኤን ሲ በ1912 ዓም ኢ ኤ አ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ከአርባ አመት በላይ ሰላማዊ የትግል ስልት ነበር ሲከተል የቆየው። ህዝባዊ እንቢታ፤ እቤት የመዋል አድማ፤ የሥራ ማቆም አድማ፤ ይለፍ ወረቀት ሳይዙ በጅምላ ሆ ብሎ የተከለከለ ቦታ ሄዶ መታሰር፤ ወዘተ…. ያሁሉ ግማሽ ምእተ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ የተካሄደው ሰላማዊ ትግል የህዳጣኑን መንግስት ጭቆናና ጭካኔ አባባሰው እንጂ ለደቡብ አፍሪካ ህዝብ የፈየደው ነገር አልነበረም።
ኋላ ላይ ግን እነማንዴላ ሀሳባቸውን ለመቀየር ተገደዱ። ሰላማዊው ትግል በትጥቅ ትግል መደገፍ እንዳለበት አመኑ። ይህንንም ወሰኑ። የሽምቅ ውጊያ ለመጀመር በርካታ የ ኤ ኤን ሲ ታጋዮች ማንዴላን ጨምሮ ወደተለያዩ ሀገሮች ለወታደራዊ ስልጠና ተሰማሩ። ማንዴላም ወደ ኢትዮጵያ አቀና። እናም እ ኤ አ በ1961 ዓም የ ኤ ኤን ሲ ወታደራዊ ክንፍ በማንዴላ መሪነት ተመስርቶ በመንግስቱ የኢኮኖሚና ወታደራዊ ተቋማት ላይ አደጋ መጣል ጀመረ።

Sunday, May 26, 2013

የሰበሩ ዝርዝር፤ ብራቮ ከንቲባ…. ብራቮ ሰማያዊ!!!

968802_418767841554502_16363769_nየሰበሩ ዝርዝር፤ ብራቮ ከንቲባ…. ብራቮ ሰማያዊ!!!
ለሚመለከተው አካል ማመልከቻ ቢያሰገባም ደብዳቤውን አንቀበልም የተባለው ሰማያዊ ፓርቲ በእማኞች ፊት ማመልከቻውን አስገብቶ ለከንቲባ ጽ/ቤትም አቤት ብሎ ነበር፡፡ እኛም ይህንን አስመልክቶ በጠዋቱ ዜና በጨዋታችን እንዲህ ብለን ነበር….
…..የጽ/ቤቱ ሃላፊዎች ለምን ደብዳቤውን አንቀበልም እንዳሉ እንጃላቸው… ምናልባት እነርሱም በመንግስታቸው የተከፉበት ጉዳ ይኖራል፡፡ (ይቺ የግዳጅ ቦንድ ግዢ እኮ ሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት ላይ ከባድ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ነው ያላት….) የምሬን ነውኮ… እነዚህ ሃላፊዎች በመንግስታቸው ላይ ቅሬታ ባይኖራቸው ኖሮ ደብዳቤውን ተቀብለው …
ለሰማያዊ ፓርቲ ባሉበት፤