Friday, May 10, 2013

አቶ መለስን የሚመጥን ጥቅስ ፍለጋ፤ “ኢህአዴግን ነፍስ ይማርልን!”

zአንዳንድ ወዳጆቻችን ልክ በህይወት ያሉ እስኪ “መስል ድረሰ መለስ ለልደትህ እንኳን አደረሰህ!… መልካም የልደት በዓል ይሁንልህ!” ሲሏቸው አይቼ ሳቅቼ ሳቅቼ ሞተውት! (ደግሞ እኮ …አንተ… ነው የሚሏቸው …ወይ ጫማ መለካካት!)


እንደ እውነቱ ስለ መለስ የልደት ቀን መታሰቢያ ለማድረግ ከኔ የሚቀድም አካል መኖር አልነበረበትም፡፡ ያ ሁሉ ወዳጅነታችን ከግባ መሬቱ ጋር አብሮ የተቀበረ አስመሰልኩት እኮ!

Sunday, May 5, 2013

! ….. በነ እስክንድር ነጋ ዙርያ ……!

https://fbcdn-profile-a.akamaihd.net/hprofile-ak-ash4/c44.45.551.551/s160x160/404269_246213892126226_1643997848_n.jpgበነ እስክንድር ነጋ … የእስር ፍርድ ምክንያት በማድረግ ስለ ጉዳዩ አስተያየት እንድሰጥ የተለያዩ የፌስቡክ ጓደኞቼ ሲወተውቱኝ ከርመዋል (የቅርብ ጓደኞቼ ግን ዝምታን መምረጥ እንዳለብኝ መክረውኛል)። አስተያየቴን እንድገልፅ የገፋፉኝ ጓዶች በቁጥር ብዙ ቢሆኑም ምክንያታቸው ወይ ዓላማቸው ግን የተለያየ ነው።

ብዙ ግዜ አስተያየቴን እንድሰጥ ከወተወቱኝ ሰዎች አብዛኞቹ የኢህአዴግ ደጋፊዎች (በፌስቡክ በሚፅፉት መሰረት) ናቸው። ለምን በነ እስክንድር ነጋ ዙርያ አስተያየት እንድሰጥ ገፋፉኝ? እኔን “ማኖ ለማስነካት” ታስቦ ነው። እኔን “ማኖ ማስነካት” እንዴት ይቻላል? ከሰዎች ጋር በማጣላት ነው። እንዴት ማጣላት ይቻላል?