አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ኢትዮጵያ የሰቆቃ ደሴት ናት አለ

የሂዩማን ራይት ዋች የአፍሪካ ዘርፍ ተጠባባቂ ዳይረክተር የሆኑት ወይዘሮ ሌዝሊ ሌፍኮ የኢትዮጵያ ባለስልጣኖች ሰላማዊ ዜጎችን አስረዉ ለማናዘዝ የሚያደርጉት ድብደባና የሚፈጽሙት ሰቆቃ እንኳን በጋዜጠኞችና በተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ላይ በጦር ወንጀለኞች ላይም ሊፈጸም የማይገባ ወንጀል ነዉና አለም ይሀንን አይነት በደል ህገ መንግስታዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ ሀሳባቸዉን በገለጹ ዜጎች ላይ ሲደርስ ዝም ብሎ መመልከት የለበትም ብለዋል። ማዕከላዊ እስር ቤት ዉስጥ የሚደረገዉ ምርመራ እስረኞችን የሚደበድብ፤ እስረኞች ዉስጥ እግራቸዉን ከተገረፉ በኋላ ለብዙ ሰዐታት በእግራቸዉ እንዲቆሙ የሚያደርግና አጥንት የሚሰነጥቅና የዘረኝነት ይዘት ያላቸዉ የቃላት ዉርጅብኝም እንደሚያጠቃልል ወይዘሮዋ የተናገሩ ሲሆን አንድ ከኦሮሚያ ክልል ተወስዶ የታሰረ ተማሪ እንደተናገረዉ ምግቡን ሲበላ ጭምር እግሩን እንደሚታሰርና እጅና እገሩን ታስሮ ለቀናት በጨለማ ቤት ዉስጥ እንደተጣለ ተናግሯል።
No comments:
Post a Comment