ህዝቡ በወያኔ ላይ ያለውን ምሬትና ጥላቻ መግለጽ ጀምሯል!

ወያኔና ጀሌዎቹ ግን ዛሬም ሊማሩ አይችሉምና ደግመው ደጋግመው ህዝባችን ሊያሞኙት ይሻሉ በ2002 አ.ም ምርጫ ቦርድ ከሚባለው ሎሊያችው ጋር ሆነው ድምጹን ሰርቀውና አሰርቀው አሽንፍዋል አሽነፍን ብለው አይናቸውን በጨው አጠበው ጨፍር ብለው አደባባይ አስወጡት፤ በጥቃቅን ስም ባደራጁቸው እበላ ባዮች ታጅበውም በአደባባይ አላገጡ በህዝብ ቁስልም ላይ ጨው ነሰነሱ ህዝብም ታዝቦ ዝም አለ ዘንድሮስ?
ዘንድሮ የተለየው ነገር ተቃዋሚዎች ተባብረው 33 የሚሆኑት በአንድ ላይ ቆሙ ከምርጫው በፊት ጥያቄዎችን አንስተው እንደራደርም ብለው ጠየቁ ትእቢተኛው ወያኔም እንደልማዱ አሻፈርኝ የት ልትደርሱ አላቸው ትኩረታቸውን በሙሉ በየቤቱ እየዞሩ ካርድ እንዲወስድ ያስፈራሩት ጀመር የፈራ ወሰደ ያልፈራም ሳይወስድ ቀረ ይህንንም ህዝብ በትዝብት ተመለከተ ፤ካድሬዎቹም ሆነ አለቆቻቸው ወያኔዎች እሁንም ህዝቡን ንቀውታል ምን ያመጣል በሚል ትእቢት ከ99.6 % ወደ 100፥ በመለወጥ ለማሸነፍና ለመጨፈርና ለማስጨፈር ዝግጅታቸውን ማጠናቅቅ ላይ ብቻ አደረጉ።