Friday, June 21, 2013

ዓባይና የአሜሪካ ጨዋታ

ዓባይና የአሜሪካ ጨዋታ

576561_4702713808339_449625552_n
መስፍን ወልደ ማርያም
ሰኔ 2005
በአሥራ ዘጠነኛው ምዕተ-ዓመት አስተሳሰብ ከዚህ ቀጥሎ የተጠቀሰው ዓላማ ለአውሮፓ ቄሣራውያን ዋና ግባቸው ሆኖ እስከሃያኛው ምዕተ-ዓመት ዘልቆአል፤ አሀን ፈጽሞ በተለየ ዘመን አሜሪካ ይህንን አስተሳሰብ ይዞ የተነሣ ይመስላል።
ኢትዮጵያን የተቆጣጠረ ዓባይን ይቆጣጠራል፤ ዓባይን የተቆጣጠረ ግብጽን ይቆጣጠራል፤ ግብጽን የተቆጣጠረ ኃይል ቀይ ባሕርን ከመግቢያና መውጫው ጋር ይቆጣጠራል፤ ቀይ ባሕርን ከመግቢያና መውጫው ጋር የተቆጣጠረ ኃይል ዓለምን ይቆጣጠራል።
አሜሪካ በግብጽ ላይ የተከለው ጥፍሩ ሲነቃነቅ መነቀሉ አለመቅረቱን ስላወቀው ሌላ የሚተክልበት አገር ይፈልጋል፤ በአካባቢው የግብጽን ነፍስ የሚነካ ከኢትዮጵያ የተሻለ አገር የለም፤ ለአሜሪካ ዓለም-አቀፍ ዓላማ ኢትዮጵያ ስትመረጥ የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም፤ በመሀከለኛው ምሥራቅ የአረቦችን የተባበረ ኃይል ለመቋቋም የተመረጡ ሦስት አረብ ያልሆኑ አገሮች — ቱርክ፣ ኢትዮጵያና ፋርስ (ኢራን) — ነበሩ፤ በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የአሜሪካ ዓለም-አቀፍ ኃይል መሰማት በጀመረበት ጊዜ ኢትዮጵያን ከከበቡአት የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ጋር የነበርዋትን የቆዩ ውዝግቦች ለመቋቋም የአሜሪካ ድጋፍ በጣም አስፈላጊ ነበር፤ አሜሪካን ከአውሮፓ አገሮች ጋር እየመዘኑና እያመዛዘኑ የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስከበር የተደረገው ዲፕሎማሲ (ዓለም-አቀፍ የሰላም ትግል) የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን መንግሥት በእውነት ከሚያኮሩት ተግባሮች አንዱ ነው፤ ይህንን ትግል አምባሳደር ዘውዴ ረታ ምስጋና ይድረሰውና የኤርትራ ጉዳይ በሚለው መጽሐፉ ግሩም አድርጎ አሳይቶናል።


ምናልባት ገና ያልተጠና ጉዳይ በዘመኑ ኢትዮጵያ የነበራት ታሪካዊ ክብር ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታሪክና ዝና ጋር ተዳምሮ በአፍሪካ ተደማጭነት ነበራት፤ ይህንን ኢትዮጵያ በአፍሪካ አገሮች ላይ የነበራትን ጫና (የዛሬውን አያርገውና) በመጠቀም አሜሪካ አፍሪካን በሙሉ ለዓላማዋ ለማሰለፍ ኢትዮጵያን መሣሪያዋ ለማድረግ ትሞክር ነበር።


እየቆየ የኢትዮጵያ መንግሥት የነጻነት መንፈስን በማሳየት ለአሽከርነት አልመች በማለቱና ለአሜሪካም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች (የእውቀት ጥበቦች) በመፈጠራቸው ኢትዮጵያ ለአሜሪካ ዓለም-አቀፍ ዓላማ አስፈላጊነትዋ በመቀነሱ አሜሪካ ኢትዮጵያን ችላ ማለት ጀመረ፤ የ1966 ግርግር ከዚህ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑን ጠለቅ ብሎ ማጥናት ያስፈልጋል፤ በዚህ መሀልም የሶቭየት ኅብረት ዓለም-አቀፋዊ ጉልበት እየተሰማ በመሄዱ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የነበረውን ዓላማ ቀስ በቀስ እየለወጠ ሄደ፤ ከዚህም ጋር የሶቭየት ኅብረት ተጽእኖ እያደገ ሄደ፤ የአሜሪካ አያያዝ እየላላ ሲሄድ የሶቭየት ኅብረት አያያዝ እየጠበቀ ሄደ፤ 1966 የአሜሪካ መውጫና የሶቭየት መግቢያ ሆነ ለማለት ይቻል ይሆናል፤ ከዚሁ ጋር አብሮ የሚታየው በኢትዮጵያ የባህላዊው ሥርዓት መሰነጣጠቅና የቆየው ትውልድ መዳከም ነው፤ የአሜሪካ መዳከም ሶቭየት ኅብረትን ሲያጠነክር፣ የአሮጌው ትውልድ መዳከም አዲሱን ትውልድ አጠነከረ፤ ይህ ማለት አሮጌው ትውልድ ከአሜሪካ ጋር የተያያዘውን ያህል አዲሱ ትውልድ ከሶቭየት ኅብረት ጋር ተያያዘ፤ የኢትዮጵያ የውስጥ ሁኔታ ብቻውን ለውጥ እንዳላመጣና ዓለም-አቀፍ ሁኔታዎችና የልዕለ ኃያላኑ ተጽእኖም ምን ያህል እንደነበረ አመላካች ነው።

ኡጋንዳ በናይል ላይ ግዙፍ የሀይል ማመንጫ መገንባት የሚያስችላትን ስምምት ተፈራረመች።

ኡጋንዳ በናይል ላይ ግዙፍ የሀይል ማመንጫ መገንባት የሚያስችላትን ስምምት ተፈራረመች።

የጥቁር አባይ ባለቤት የሆነቸው ኢትዮጵያ የአባይን ግድብ ለመስራት ደፋ ቀና ስትል ግብጽ ተደናግጣ የምትገባበት ጠፍቷት በዲፕሎማሲው መስክ እና በማስፈራራቱ ሜዳ ተወጥራ በምትገኝበት በአሁን ወቅት የነጭ አባይ ባለቤት አንዷ ኡጋንዳ በናይል ወንዝ ላይ ግዙፍ በ1 ነጥብ 65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገነባው 600 ሜጋ ዋት የሀይል ማመንጫ”ካሩማ” የተባለ ግድብ መገንባት የሚያስችላትን ስምምነት ከቻይናው ሲኖ ሀይድሮ ግሩፕ ከተባለ ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራርማለች።
ካሩማ ግድብ ከግንባታው በተጨማሪ 1 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሀይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታን ያካትታል::
ደቡብ ሱዳን እንዲሁ በናይል ወንዝ ላይ የኤሌክትሪክ

የኛ ነገር፡ የአባይ ችግር፡ የአያልሰው ምክር (ተክሌ፤ ከተረንቶ)

የኛ ነገር፡ የአባይ ችግር፡ የአያልሰው ምክር (ተክሌ፤ ከተረንቶ)

June 21, 2013 ክፍል 4 (ክፍል ሁለትና ሶስት ይመጣሉ)
ተክሌ፤ ከተረንቶ

1. ብዜ ግዜ የአቶ አያልሰው ደሴ ጽሁፎች ረዣዥሞች ስለሆኑ፤ እንዲሁም ክፍል ስለሚበዛቸው (1፣ 2፣ 3፣ 4፣ … )፤ ርእሳቸውን ብቻ እያየሁ አልፋቸው ነበር። በዚህ በአባይ ጉዳይ ግን የጻፉት አነበብኩት። ጽሁፉ በርስ በርስ ቅራኔ የሚንተከተክና በኢህአዴግ የአባይ ግድብ ማጭበርበሪያ ዘመቻ ዙሪያ ያለውን ተቃውሞ በቅጡ ያልዳሰሰ፡ ይልቅስ ሌሎችን ተቺዎች በሚከስበት ደዌ ክፉኛ የታመመ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በተጨማሪም ጽሁፉ የአካባቢውን ፖለቲካ በቅጡ የቃኘ ቢሆንም፤ የደረሰባቸው ድምዳሜዎች ግን የተሳሳቱ ናቸው።
2. እንደምንም በርትቶ እዚያ ለደረሰ ሰው፤ የአቶ አያልሰው ደሱ ጽሁፍ ዋና ሀሳብ በክፍል ሁለት፤ በአምስተኛው ገጽ፤ በሁለተኛ አንቀጽ ላይ ይገኛል።

«ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ግንባር» የሚል ስም ይኖረናል – ሌንጮ ባቲ

«ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ግንባር» የሚል ስም ይኖረናል – ሌንጮ ባቲ


የቀድሞ የኦነግ መስራችና አመራር አባላት በብዛት ያሉበት፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፎረም በሚል ስም፣ አንድ ድርጅት መቋቋሙ ይታወቃል።  ድርጅቱ የመገንጠል ጥያቄ ጎጂና ጠቃሚ እንዳልሆነ በማተት የኢትዮጵያን አንድነትና ሉአላዊነት በጠበቀ መልኩ የሁሉም መብት የሚከበርባትን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንደሚታገልም ገልጾ ነበር። «ለኦሮሞዎች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የኢትዮጵያዉያን መብት እንታገላለን» ያለዉ ኦዴፍ ፣ የአመራር አባላቱ በተለያዩ ፎረሞች በመገኘት ፕሮፖዛሎቻቸውን እያቀረቡ ሲሆን፣ ከተለያዩ ድርጅቶችም ጋር እየተናገገሩ መሆናቸውንም ይናገራሉ።

ቡልቻ ደመቅሳ፡- ‹አንድነት› ፓርቲ የገዢዎች ልጆች ናቸው

ሰንደቅ፡- በመጨረሻ የእርስዎ ባለቤት ግብፃዊ መሆናቸው ይነገራል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ ግብፅና ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ

ቡልቻ ደመቅሳ፡- ‹አንድነት› ፓርቲ የገዢዎች ልጆች ናቸው

ላይ እየተገነባ ባለው የህዳሴው ግድብ ላይ አለመግባባት ተፈጥሯል። ይህ ጉዳይ በእርስዎ ቤተሰብ ላይ ምን ስሜትን ፈጠረ?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- ባለቤቴ ሙሉ በሙሉ ግብፃዊት አይደለችም። አባቷ የትግራይ ሰው ሲሆኑ እናቷ የግብፅ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ናቸው። መቼም ባልና ሚስት የሚያወራውን ለሌላ ሰው አይነገርም፤ ምስጢር ነው። በአባይ ጉዳይ ያለን አስተያየት ግን አንድ ነው። ግብፆች መገንዘብ ያለባቸው ኢትዮጵያ ወንዙን መጠቀም የፈለገችው ከወንዙ ላይ ቆንጥራ ነው። ምናልባት እኛ የምንወስደውን ውሃ ግብፅ የምታባክነውን ሊሆን ይችላል። እኛ ውሃውን ለሃይል ማመንጫ እንጂ ለመስኖ አይደለም። ኢትዮጵያ መብቷን መጠቀም ከፈራች ትጠፋለች። ስለዚህ የቅኝ ግዛት የውሃ ስምምነቱን ሁላችንም እየተቃወምን የግብፅን ሕዝብ ሳንጎዳ መጠቀም አለብን።
* ዶ/ር ነጋሶ….. <አማራም ቢሆኑ ውስጡ ገብቼ አንድነትን አጠናክራለው> የሚል አቋም አላቸው።
* አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞነት አለባቸው ይባላል። ኦሮሞነት ስላላቸው የኦሮሞን ታሪክና ባህል አላቸው ማለት ግን አይደለም…..
* ቡልቻ “አማራ” የሚለውን ቃል ተጠቀመ ብለው [አንድነቶች] ሊከፋቸው አይገባም። ታዲያ እኔ ምን ብዬ ልግለጣቸው? እዛ ያሉትን እኔ የማውቃቸው በአማራነታቸው ነው።
* በአንድነት ውስጥ ያሉ አማራዎች ግን የጀነራል፣ የሀገረ ገዢ፣ የአምባሳደር የአስተማሪና የሲቪል ሰርቪስ ልጆችና የልጅ ልጆች ናቸው።


Thursday, June 20, 2013

አቶ ኦባንግ ሜቶ ኢትዮጵያውያን አሜሪካ ነጻ ታወጣናለች ብለው እንደማይጠብቁ፣ የራሳቸውን መብት በራሳቸው ለማስከበር እንደሚችሉ ገልጸው፣( video )

አቶ ኦባንግ ሜቶ ኢትዮጵያውያን አሜሪካ ነጻ ታወጣናለች ብለው እንደማይጠብቁ፣ የራሳቸውን መብት በራሳቸው ለማስከበር እንደሚችሉ ገልጸው፣( video )

ኢሳት ዜና:- የአፍሪካ ጉዳዮች ሃላፊ ዶናልድ ያማማቶ፣ በአፍሪካ የዩሴ አይ ዲ ዳይሬክተር ኤሪል ጋስት፣ በአፍሪካ ጉዳዮች ተመራማሪ ዶ/ር ፒተር ፓሀም፣ የግንቦት7 ሊቀመንበር ዶ.ር ብርሀኑ ነጋ ፣ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶና የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የአሜሪካ ተወካይ ሚስተር አዶቲ አኪዌ እና ሌሎችም ታዋቂ ምሁራን ፖለቲከኞች የተሳተፉበት ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ አምባሳደር ያማማቶ እና ዶ/ር ጋስት ኢትዮጵያ በመስቀለኛ መንገድ ላይ እንድምትገኝ ገልጸዋል።
የኢህአዴግ መንግስት የኢኮኖሚ እድገት ማምጣቱን የገለጹት አምባሳደር ያማማቶና ሚስተር ጋስ፣ በሌላ በኩል ግን መንግስት ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብቶች ረገጣ በመፈጸሙ የአገሪቱን መጻኢ እድል አደጋ ላይ ጥሎታል ብለዋል።
ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ፣ አቶ ኦባንግ ሜቶ እና ሚ/ር አክዌ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን፣ ዶ/ር ብርሀኑ ከአቶ መለስ ሞት በሁዋላ ያለው የኢትዮጵያ ሁኔታ በመለስ ጊዜ እንደነበረው ምናልባትም ከዚያ በበሳ ሁኔታ አስከፊ እየሆነ መሄዱን ገልጸዋል። የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከፍተኛ ገንዘብ የዘረፉ እና ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የፈጸሙ በመሆናቸው እንጠየቃለን በሚል ፍርሀት ስልጣን በቀላሉ ለመልቀቅ እንደማይፈልጉ ዶ/ር ብርሀኑ አክለዋል።
ዶ/ር ብርሀኑ መንግስትን በሀይል ለማውረድ የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች እየተጠናከሩ መሄዳቸውን፣ አገሪቱ ወደ አልተፈለገ ግጭት ከማምራቷ በፊት የአሜሪካ መንግስት አሁን የሚከተለውን ፖሊስ ቆም ብሎ እንዲፈትሽ አሳስበዋል። አቶ ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው ኢትዮጵያውያን አሜሪካ ነጻ ታወጣናለች ብለው እንደማይጠብቁ፣ የራሳቸውን መብት በራሳቸው ለማስከበር እንደሚችሉ ገልጸው፣ አሜሪካ ከአምባገነኑና ዘረኛው የህወሀት መንግስት ጋር የምታደርገውን ግንኙነት እንደገና እንድትፈትሽ ጠይቀዋል።
የውይይቱ ሊቀመንበር የተከበሩ ሚስተር ክሪስ ስሚዝ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በዝርዝር ለተሰብሳቢው አቅርበዋል።http://www.youtube.com/watch?feature=player_embedded&v=pBVp6a3rSUc

ግብፅ የህዳሴውን ግድብ በአየር ማጥቃት የሚያስችል አቅም የላትም ስትራትፎር

ግብፅ የህዳሴውን ግድብ በአየር ማጥቃት የሚያስችል አቅም የላትም ስትራትፎር

ግብፅ የኢትዮጵያን ሕዳሴ ግድብ በአየር ለማጥቃት ከኢትዮጵያ ያላት የአየር ርቀት ይገድባታል ሲል ስትራትፎር የተባለው መሠረቱን በአሜሪካ አገር ያደረገ ጂኦፖለቲካ እና ሴኩሪቲ ምርምርና ጥናት የሚያደርግ ተቋም በድረ ገጽ አስነብቧል።
 

ተቋሙ ባሰራጨው ትንታኔ ላይ እንዳሰፈረው፤ “በሁለቱ ሀገሮች መካከል ያለው የአየር ርቀት ለግብፅ ጦር ሰራዊት ሁኔታዎችን አስቸጋሪ ያደርገዋል” ብሏል። ተቋሙ አያይዞም፤ “ግብፅ አየር በአየር ነዳጅ የሚቀባበሉ ተዋጊ የጦር ጀቶች ባለቤት ለመሆን ያደረገችው የአቅም ግንባታ የለም። አሁን በግብፅ አየር ኃይል እጅ የሚገኙ የጦር ጀቶች ከግብፅ አየር ሃይል በመነሳት በተወሰነ የአየር ክልል ውስጥ የማጥቃት አቅም ያላቸው እንጂ በጣም ብዙ ርቀት በመጓዝ ማጥቃት የሚችሉ አይደሉም” ሲል የግብፅን የአየር ጥቃት አቅምን አጋልጧል። “ግብጾች ትንሽ ያላቸው መፅናኛ የሕዳሴው ግድብ ለሱዳን ድንበር የቀረበ መሆኑ ነው። የሱዳን የአየር ሃይል ቤዝ መጠቀም ከቻሉ አንዳንድ የግብፅ የጦር ጀቶች ማጥቃት በሚችሉበት ራዲየስ ውስጥ የህዳሴው ግድብ ሊወድቅ ይችላል። ሆኖም ግን ከሱዳን ግዛት ውስጥ በመነሳት የሚደረግ የአየር ጥቃት ውስብስብ የፖለቲካ አደጋዎች ያስከትላል። በዓለም ዓቀፍ መድረክም ሱዳንና ግብፅ ውጤቱን ተከትሎ የሚከፍሉት ዋጋ ይኖራል። ሱዳን ለኢትዮጵያ የድንበር ተጋሪ ከመሆኗ አንፃር ከኢትዮጵያ መንግስትም በሚሰነዘር ቀጥተኛ ወታደራዊ ጥቃት ተጋላጭ መሆኗ አይቀርም” ሲል ተቋሙ በትንታኔው አስነብቧል።
ሌላው የግብጾች አማራጭ ልዩ የጦር ሰራዊት ኮማንዶ ማሰማራት ነው ያለው ተቋሙ፤ ይህም ቢሆን የራሱ የሆነ ችግሮች አሉት።


ግድብ ወሳኝ መሰረተ ልማት ከመሆኑ አንፃር የማያቋርጥ ጥበቃ የሚደረግለት ነው። በአብዛኛው ቋሚ የጦር ሰራዊት ጥበቃ ይደረግለታል። ኢትዮጵያም የተለየች አይደለችም፤ ይህንኑ ጥበቃ ታደርጋለች። ስለዚህም ግድቡ ላይ አደጋ ለማድረስ የግብፅ ልዩ ኮማንዶ ኃይል እድል እና ክህሎት ሊኖረው ይገባል። ሆኖም ይላል፣ ትንሽ ቁጥር ያለው የኮማንዶ ሃይል ምንም ያህል ክህሎት ቢኖረውም መሰረታዊ አደጋ የማድረስ አቅሙ ዝቅተኛ ነው ሲል ስልቱን ያጣጥለዋል። የሱዳን መንግስት በበኩሉ በመንግስት ቃል አቀባዩና በማስታወቂያ ሚኒስትር በኩል ለሕዳሴው ግድብ ያለውን ድጋፍ በይፋ ከማረጋገጡም በላይ ሱዳን በሕዳሴው ግድብ ተጠቃሚ ትሆናለች ሲል ማስታወቁም ይታወሳል።


ስትራትፎር የሚባለው ተቋም ከአሜሪካ መንግሥት የስለላ ድርጅቶች እና የባሕር ኃይል ተቋማት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ይታወቃል። በፋኑኤል ክንፉ የሰንደቅ ጋዜጣ

ከእናንተ ከዳኞቹና የሞት ፍርድ እንድትበይኑብኝ ካዘዛችሁ ሰው ይልቅ እኔ ፍርድ ተቀባይ የዛሬ ወንጀለኛ የነገ ባለታሪክ ነኝ፡፡

ከእናንተ ከዳኞቹና የሞት ፍርድ እንድትበይኑብኝ ካዘዛችሁ ሰው ይልቅ እኔ ፍርድ ተቀባይ የዛሬ ወንጀለኛ የነገ ባለታሪክ ነኝ፡፡

መንግስቱ ንዋይ : መጋቢት 19 ፣ 1953 ዓ.ም የሞት ፍርድ ከተወሰነባቸው በኋላ የተናገሩት ንግግር
እናንት ዳኞች የበየናችሁብኝን የሞት ፍርድ ያለ ይግባኝ ተቀብያለሁ፡፡ ይግባኝ ብየ ጉዳየን የሚመለከትልኝ የኢትዮጵያ ህዝብ ቢሆን ኖሮ ይግባኝ


ማለት በፈለግሁ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ እንደማይሆን አውቃለውና በይግባኝ የአፄ ኃ/ስላሴን ፊት ማየት አልፈቅድም፡፡ በእግዚያብሄር ስም ተሰይማችሁ ከተቀመጣችሁበት የፍርድ ወንበር ላይ ከመቀመጣችሁ በፊት በእኔ ላይ የምትሰጡትን የዛሬውን ፍርድ ታውቁት እንደነበር ሳስብና
ፍርድ እስከዚህ መርከሱን ስታዘብ ሀዘኔ ይበዛል፡፡

የደቡብ አፍሪካ ጋዜጦች ከኢትዮጵያ ቡድን ላይ 6 ነጥብ ይነሳ በሚል ዘመቻ ይዘዋል

በፊፋ ህግ መሰረት የተቀጣ ተጨዋች ያላግባብ ገብቶ የተጫወተበት ጨዋታ ውጤት ይሰረዝና ከቡድኑ ላይ 3 ነጥብ ተቀንሶ ጨዋታው በ 3-0 ወጤት ይመዘገባል።

ኢትዮጵያ ከቦትስዋና ጋር ስትጫወት ምንያህል ያላግባብ ተሰልፏል በዚህ ምክንያት ከኢትዮጵያ ላይ 3 ነጥብ ይነሳል። ይሁንና ከቦትስዋና ጨዋታ በሗላ ፊፋ በፍጥነት በጉዳዩ ጣልቃ ስላልገባ ምንያህል እንደገና ከደቡብ አፍሪካ ጋር በነበረው ጨዋታ ተሰልፏል፣ ይህንን በተመለከተ በጠራ ሁኔታ በፊፋ ህግ ላይ የተቀመጠ ነገር የለም። ስለዚህ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በፊፋ ባለስልጣኖች እጅ ላይ ወድቋል ማለት ነው።
የደቡብ አፍሪካ ስፖርት ጋዜጠኞች፣ ጡረታ ዳኞች፣ ጡረታ የብሄራዊ ቡድን ታዋቂ ተጫዋቾች ከፍተኛ ዘመቻ ይዘዋል “ከኢትዮጵያ ቡድን ላይ 6 ነጥብ ይቀነስ” ነው የሚሉት። በፊፋ ባለስልጣናት ውሳኔ ላይ ጫና ለማሳደር ነው ጥረታቸው።

 
በኢትዮጵያ በኩል ተመሳሳዩን ለመከወን በፖለቲካ አመለካከታቸው ለገዢው ቡድን ታማኝ በመሆናቸው ብቻ ቦታውን የያዙት ጋዜጠኞች እና የስፖርቱ ባለስልጣናት ብቃት ያላቸው አይመስልም።
የደቡብ አፍሪካ ጋዜጦች ከኢትዮጵያ ቡድን ላይ 6 ነጥብ ይነሳ በሚል ዘመቻ ይዘዋል

የደቡብ አፍሪካ ጋዜጦች ከኢትዮጵያ ቡድን ላይ 6 ነጥብ ይነሳ በሚል ዘመቻ ይዘዋል

June 20, 2013
በፊፋ ህግ መሰረት የተቀጣ ተጨዋች ያላግባብ ገብቶ የተጫወተበት ጨዋታ ውጤት ይሰረዝና ከቡድኑ ላይ 3 ነጥብ ተቀንሶ ጨዋታው በ 3-0 ወጤት ይመዘገባል።

ኢትዮጵያ ከቦትስዋና ጋር ስትጫወት ምንያህል ያላግባብ ተሰልፏል በዚህ ምክንያት ከኢትዮጵያ ላይ 3 ነጥብ ይነሳል። ይሁንና ከቦትስዋና ጨዋታ በሗላ ፊፋ በፍጥነት በጉዳዩ ጣልቃ ስላልገባ ምንያህል እንደገና ከደቡብ አፍሪካ ጋር በነበረው ጨዋታ ተሰልፏል፣ ይህንን በተመለከተ በጠራ ሁኔታ በፊፋ ህግ ላይ የተቀመጠ ነገር የለም። ስለዚህ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በፊፋ ባለስልጣኖች እጅ ላይ ወድቋል ማለት ነው።

የደቡብ አፍሪካ ስፖርት ጋዜጠኞች፣ ጡረታ ዳኞች፣ ጡረታ የብሄራዊ ቡድን ታዋቂ ተጫዋቾች ከፍተኛ ዘመቻ ይዘዋል “ከኢትዮጵያ ቡድን ላይ 6 ነጥብ ይቀነስ” ነው የሚሉት። በፊፋ ባለስልጣናት ውሳኔ ላይ ጫና ለማሳደር ነው ጥረታቸው።
በኢትዮጵያ በኩል ተመሳሳዩን ለመከወን በፖለቲካ አመለካከታቸው ለገዢው ቡድን ታማኝ በመሆናቸው ብቻ ቦታውን የያዙት ጋዜጠኞች እና የስፖርቱ ባለስልጣናት ብቃት ያላቸው አይመስልም።
Ethiopia could lose six points for also fielding their suspended player against Bafana.

ቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን!


ቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን!

እስከዛው ድረስ ግን፤ ቀኑ እስኪሞላ የስደኞችን ቀን እኛ ስናከብረው “ቀን የጎደለብን…” የሚለውን ከፊት ለፊቱ ጨምረን “ቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን” ብለን ነው ማለት ነው !
Boat_loaded_with_Ethiopian_and_Somali_immigrants_in_the_Gulf_of_Aden_yemenቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን!
ዛሬ የስደተኞች ቀን መሆኑን ወዳጄ ሰሚር ፌስ ቡክ ላይ ባጋራን ማስታወሻ እና የአልጀዚራ ድረ ገፅ ማስፈንጠሪያ አስታወስኩ፡፡ አንዳንዱ ቀን “እንኳን አደረሳችሁ” ተባብሎ ቢቻል ጠላ ተጠምቆ ድፎ ዳቦ ተደፍቶ እና ዶሮ ወጥ ተወጥውጦ ያከብሩታል፡፡ አንዳንዱ ቀን ደግሞ በሀዘን “ምን ይሻላል ምን ይበጃል” የሚለውን እያንጎራጎሩ ያከብሩታል፡፡ ታድያ “ቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን” በተለይ ለእኛ ኢትዮጵያያን የሀዘን ቀናችን አይደለምን!?

በኢትዮጵያ ከፍተኛውን ኢንቨስተር መንግስት ነው ሲል የአለም ባንክ አስታወቀ

በኢትዮጵያ ከፍተኛውን ኢንቨስተር መንግስት ነው ሲል የአለም ባንክ አስታወቀ

ኢሳት ዜና:- ባንኩ  በገንዘብና የ ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር አነሳሽነት ያጠናቀረውን ሪፖርት  በሸራተን አዲስ ይፋ ሲያደርግ የኢትዮጵያ መንግሥት በዓለም በከፍተኛ መጠን ኢንቨስት ያደርጋሉ ከሚባሉ ሦስት መንግሥታት መካከል  እንደሆነ ፤በ አንፃሩበግል ዘርፉ የሚካሄደው   ኢንቨስትመንት የ ኣለማችን ስስድስተኛው ዝቅተኛ  ኢንቨስትመንት መሆኑን አመልክቷል፡፡
እንደ ሪፖርተረ  ዘገባ፤ የባንኩ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጉዋንግ ቼንግና የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር አብርሃ ተከሰተ በተገኙበት በሸራተን አዲስ ይፋ የተደረገው የዚህ ሪፖርት ዋነኛ  ትኩረት መንግሥት በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ሚና የሚመለከት ነው።

Wednesday, June 19, 2013

የዓባይ ጉዳይ እኛ ዜጎችም ያገባናል።

የዓባይ ጉዳይ እኛ ዜጎችም ያገባናል።
It is so!!!
Abraha Desta
ግብፅና ኢትዮዽያ በዓባይ ግድብ ጉዳይ የቃላት ጦርነት ከከፈቱ ሰንብተዋል። ዓባይ ወንዝ ታሪካዊ ከመሆኑ የተነሳ የሁለቱም ሀገሮች እሰጣገባም ታሪካዊ መንስኤ አለው። ኢትዮዽያ የዓባይ ወንዝ አቅጣጫ መቀየሯ በተሰማ ማግስት የግብፅ ፖለቲከኞች (አንድም ተደናግጠዋል አልያም የህዝብ ስሜት ለማስቀየር ፈልገዋል) አላስፈላጊ የማስፈራርያ ቃላት መሰንዘር ጀመሩ። የኢትዮዽያ የትእግስት መልስ ወደነዋል።

የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያውያን ለመብታቸው መከበር የሚያሰሙትን ድምጽ ይሰማል ሲሉ ወ/ሮ አና ጎሜዝ ተናገሩ

የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያውያን ለመብታቸው መከበር የሚያሰሙትን ድምጽ ይሰማል ሲሉ ወ/ሮ አና ጎሜዝ ተናገሩ

ana
ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ አባል የሆኑት እና በምርጫ 97 ወቅት የህብረቱ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የነበሩት ወ/ሮ አና ማርያ ጎሜዝ ይህን የተናገሩት ኢትዮጵያውያን ዛሬ በአውሮፓ ህብረት መቀመጫ ፊትለፊት ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ነው ። ወ/ሮ አና ጎሜዝ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያውንን ጩሀት ሰምቶ መልስ እንደሚሰጥ ተናግረው፣ በግላቸው ከኢትዮጵያውያን ጎን ቆመው ለውጥ እስከሚመጣ እንደሚታገሉ ተናግረዋል።
በተቃውሞው ላይ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ውስጥ እየደረሰ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ዘርዝረው ለአውሮፓ ህብረት ባለስልጣናት አቅርበዋል። ከተቃውሞ ሰልፉ አዘጋጆች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ሻውል ሰልፉ የተሳካ እንደነበር ገልጸዋል።

ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንና የዘረኛው ወያኔ ሹመኞች

ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንና የዘረኛው ወያኔ ሹመኞች

June 19, 2013

በሰው ቁስል ላይ ጨው እየነሰነሱ የክርስቲያን ሥራ እየሰራሁ ነው ማለት አይቻለም።
በስመ አብ፤ ወወልድ፤ ወመንፈስ ቅዱስ፤ አሃዱ አምላክ፤ አሜን።
በ09/06/2013 በዕለተ እሑድ ለንደን በሚገኘው የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከቅዳሴ በኋላ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደርና ሹማምንቶች የሚቀጥለውን ማስታወቂያ ለሕዝቡ አስተላልፈዋል።
  1. በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ላለፉት ሦስት ወራት መዘጋቷን፤
  2. ለብጥብጡና ለችግሩ መንስዔ የሆነው ቤተ ክርስቲያኗ ኢትዮጵያ በሚገኘው በቅዱስ ሲኖዶስ ሥር ባለመመራቷ መሆኑን፤
  3. ቤተ ክርስቲያኗ ላለፉት 7 ዓመታት ኢትዮጵያ ከሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ ተነጥላ ብቻዋን ስትንከራተት ከቆየች በኋላ አሁን ተመልሳ መቀላቀሏን። (ማስታወቂያው ከተነገረ በኋላ እንደ ተለመደው ሕዝቡ የሚጠበቅበትን ጭብጨባና እልልታ እንዲያሰማ ተደረገ)
  4. ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ችግር መንስዔ የሆነው ጉዳይ እልባት ሊያገኝ የቻለው ከቅዱስ ሲኖዶስ ተልከው በመጡት በሊቃነ ጳጳሳቱ መሆኑንና የሰጡት መፍትሔም ቤተ ክርስቲያኗ በአቡነ እንጦስና በመጋቢ ተወልደ በሚመራው የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሃገረ ስብከት ሥር እንድትደዳደር መመሪያ ሰጥተው ወደ ኢትዮጵያ መለሳቸው ነው በማለት አብራርተዋል።

“ሁለት ሳምንት አለፈ። ጥያቄዎቻችን አልተመለሱም።” ክዳኮታ የጥናት ማእከል

“ሁለት ሳምንት አለፈ። ጥያቄዎቻችን አልተመለሱም።” ክዳኮታ የጥናት ማእከል

Share
“ኢትዮጵያችንን ዲሞክራሲያዊና የዜጎች መብት የሚከበርባት አገር የማድረግ ቀድምን የጀመርነው ትልቅ ውጥን አለ”።ማንም ይበለው አባባሉ የበዛእውነትና ትክክለኛነትየያዘ ስለሆነ አብዝተንወደነዋል። ያለንበትን ጠቅላል ሁኔታ ከዚህ የተሻለ የሚገልጽና ልንጽፍ ላሰብነው የሚሆን አርስት ማግኝትንብናስብም አላገኘንም። ስላልሆነ ኮርጀንዋል።
ከሁለት ሳምንት በፊት ብዙ ሆነን አደባባይ ወጥተን በጣም ቀላል የሆኑ የመብት ጥያቄዎቻችንን አቅርበናል። አጥጋቢ በሆነ ሁኔታ ለጥያቄያችን መልስ ካልተሰጠን በሶስት ወር ውስጥ እጅግ በዝተን አደባባይ ደግመን እንወጣለን ብለናል። ወያኔ አክብሮን ለጥያቄዎቻችን መልስ የሚሰጥ አይመስልም።ስለዚህም ሰላማዊ የደባባይ ተቃውሟችን ቀጠሮ እንደተጠበቀ ነው ማለት ነው።
Read more in PDF.

የግለሰቦች እንዝላልነት ቡድኑን ዋጋ አስከፍሏል ለድረገፅ ጥገኛ ጋዜጠኞቻችን ውድቀት ሆኗል ዋልያዎቹ የአለም ዋንጫ እድል በእጃቸው ይገኛል

የግለሰቦች እንዝላልነት ቡድኑን ዋጋ አስከፍሏል ለድረገፅ ጥገኛ ጋዜጠኞቻችን ውድቀት ሆኗል ዋልያዎቹ የአለም ዋንጫ እድል በእጃቸው ይገኛል

http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/06/ethiopia-bafana-bfana.jpg በቆንጂት ተሾመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን አሁንም ደጋፊዎቹን በደስታ ያሳበደ ውጤትን በአዲስ አበባ ስታዲየም አስመዝግቧል። እሁድ እለት የደቡብ አፍሪካ አቻውን 2ለ1 በማሸነፍ ለብራዚሉ የአለም ዋንጫ የመጨረሻ ምዕራፍ ማለፉ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ከመጠን በላይ አስፈንጥዟል። ለብዙዎችም ውጤቱ ለማመን የሚከብድ ስለነበር ደስታውና ፈንጠዝያው ልክ አልነበረውም። ዋልያዎቹን ለመደገፍ በአዲስ አበባ ስታዲየም ዙሪያ ተሰልፎ ያነጋው ተመልካች አንገቱን ደፍቶ አለመመለሱ ራሱ እጅግ የሚያስደስት ነው።

የዘናጭ ልጅ ልቅሶ

የዘናጭ ልጅ ልቅሶ


click here for pdf
እናቱ ለአሥራ አምስት ዓመት ልጇ የአክስቱን ሞት እንዴት እንደምትነግረው ተጨንቃለች፡፡ ይህቺ የአባቱ እኅት የሆነችው የልጁ አክስት ልጅ አልነበራትምና እንደ ልጇ ታየው ነበር፡፡ አብራው ኳስ ታያለች፤ አብራው ትዝናናለች፣ አብራው ታጠናለች፣ አብራው ትዋኛለች፣ አብራው ፊልም ታያለች፣ አብራው ኳስ ትጫወታለች፡፡
እንዲህ የምትሆንለትን አክስቱን ሞቷን ሲሰማ ያብዳል ብላ እናቱ ተጨንቃለች፡፡ እናም ትንቆራጠጣለች፡፡ ከትምህርት ቤት ሲመጣ መጀመርያ መክሰስ አበላችውና ወደ መኝታ ቤት ወሰደችው፡፡ ከዚያም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ መኖርና መሞት ያለ መሆኑን፤ አንዳንድ ጊዜ የምንወዳቸው ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ትነግረው ጀመር፡፡ ልጁ ግራ ገባው፡፡
‹እይውልህ ልጄ› አለች እናቱ ድምጽዋ ሆድዋ ውስጥ ገብቶ ሊጠፋ እየደረሰ፡፡ ‹‹ያች የምትወድህና የምትወዳት አክስትህ በድንገት ትናንት ማታ ዐረፈች›› አለችው

የኤርትራውያን በኢትዮጵያ መንሰራፋት አሳሳቢ እና አደገኛ ነው!!! (ሊነበብ የሚገባው!!)

የኤርትራውያን በኢትዮጵያ መንሰራፋት አሳሳቢ እና አደገኛ ነው!!! (ሊነበብ የሚገባው!!)

ምንሊክ ሳልሳዊ ብሎግ
‹‹ሁለት እግሮች አሉኝ ብሎ ሁለት ዛፍ ላይ መውጣት አይቻልም›› ተብሏል፡፡ ትናንት ‹‹ወገኖቼ እንኳን ደህና መጣችሁልኝ›› ብሎ የተንከባከባቸውን ሕዝብን ዓይንህን ላፈር ያሉት፣ ፀባችን ከመንግሥትና ከሥርዓት ጋር ነው ሲሉ ቆይተው ጊዜ ሲያመቻቸው ሕዝቡን እንደበደላቸው ጠላት የረገሙት ሰዎች፣ ዛሬ ደግሞ አይ ለጥቅማችን ሲሆንማ እንፈልግሃለን ያለህን ደግ ነገር አጋራን ያውም በእኩል ባለመብትነት ሲሉት ምን ይሰማቸዋል? ኢትዮጵያውያንስ እንዴት እንዲመለከቷቸው ይመኛሉ? ኤርትራ 

ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለኢትዮጵያ አዲስ አምባሣደር አጩ

ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለኢትዮጵያ አዲስ አምባሣደር አጩ

አምባሣደር ፓትሪሽያ ኤም ሃስላች
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለኢትዮጵያ አዲስ አምባሣደር አጩ፡፡
ፕሬዚዳንቱ በአምባሣደርነት እንደሚልኳቸው ትናንት ስማቸውን ይፋ ካደረጓቸው ስድስት አዳዲስ ተሽዋሚዎች መካከል በኢትዮጵያ መጭዋ አምባሣደር እንዲሆኑ የታሰቡት ፓትሪሽያ ኤም ሃስላች አንዷ ናቸው፡፡
አምባሣደር ሃስላች አሁን እየሠሩ ያሉት በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የግጭቶችና ማረጋጋት ሥራዎች ማስተባበሪያ የሆነው አዲስ ቢሮ ዋና ምክትል ረዳት ሚኒስትር ሆነው ነው፡፡


አምባሣደር ሃስላች የአሜሪካው “መጭውን ትውልድ መመገብ – Feed the Future” የሚባለው የዓለም አቀፍ ረሃብ ማስወገጃና የምግብ ዋስትና መርኃ ግብር በውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ውስጥ የዲፕሎማሲ አስተባባሪም ነበሩ፡፡
ሚስ ሃስላች በፓኪስታን የዩናይትድ ስቴትስ የምጣኔ ኃብት ቆንሲል፣ በኢንዶኔዥያና በናይጀሪያ ደግሞ ምክትል ቆንሲል ሆነው አገልግለዋል፡፡


በዩናይትድ ስቴትስ ግብርና ሚኒስቴር ውስጥ ይሠሩ በነበረት ጊዜም በሕንድ የአሜሪካ የአካባቢው ሃገሮች አታሼ ሆነው ሠርተዋል፡፡
እአአ ከ2004 እስከ 2007 ዓ.ም በላኦስ ሕዝባዊት ዴሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ እና ከ2007 እስከ 2009 ዓ.ም ለነበሩት ዓመታትም በእሥያ-ፓሲፊክ የምጣኔ ኃብት ትብብር መድረክ /አፔክ/ የአሜሪካ አምባሣደር ሆነው አገልግለዋል፡፡
አምባሣደር ፓትሪሽያ ሃስላች በኢራቅና በአፍጋኒስታንግ ግዙፍ የሆኑ የአሜሪካ መርኃግብሮችን መርተዋል፡፡
በኦሬገን ግዛት ሌክ ኦስዌጎ የተወለዱት ሚስ ሃስላች ከዋሽንግተኑ ጎንዛጋና ከኒው ዮርኩ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ባችለርስና ማስተርስ ዲግሪዎቻቸውን አግኝተዋል፡፡
ሚስ ፓትሪሽያ ሃስላች ሽሪን እና ኪራን ኧርበርት የሚባሉ ሁለት ሴት ልጆች እናት ናቸው፡፡
ዴቪድ ሺን - በኢትዮጵያ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሣደር እና በዋሽንግተን ዲሲው ጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ የዓለምአቀፍ ግንኙነቶች ረዳት ፕሮፌሰር
ዴቪድ ሺን – በኢትዮጵያ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሣደር እና
በዋሽንግተን ዲሲው ጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ የዓለምአቀፍ ግንኙነቶች ረዳት ፕሮፌሰር
አምባሣደር ሃስላች “በሕይወት ዘመን አንዴ ሊገኝ የሚችል ቆንጆና ድንቅ ሃገርን ለማየት የታደሉ ሰው መሆናቸውንና ኢትዮጵያ ብዙ ሊሠሩባቸው የሚችሉ ችግሮች ያሉባት ሃገር”ም መሆኗን ለቪኦኤ በመግለፅ ስለምሥራቅ አፍሪካ ሰፊ ዕውቀት ያላቸው ቀድሞ በኢትዮጵያ አምባሣደር ሆነው ያገለገሉት በዋሽንግተን ዲሲው ጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ የዓለምአቀፍ ግንኙነቶች ረዳት ፕሮፌሰር ዴቪድ ሺን ለአዲሷ አምባሣደር መልካሙን ሁሉ ተመኝተዋል፡፡


የአምባሣደር ፓትሪሽያ ኤም ሃስላች ሹመት በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ከፀደቀ አዲሱን ሥራቸውን አዲስ አበባ ላይ በአዲሱ 2006 ዓ.ም መስከረም ውስጥ ይጀምራሉ፡፡

ኢትዮጵያ እና ዴሞክራሲ

ኢትዮጵያ እና ዴሞክራሲ

June 18, 2013 ዞን9 ብሎግ
ዴሞክራሲ ምንድን ናት? የዴሞክራሲ መናስ እንዴት ትወርዳለች? እንደምንስ ትፀናለች? የዲሞክራሲ ዋነኛ ጠላቶችስ እነማን ናቸው? የሚሉት ጥያቄዎች ለረጅም ዘመናት በየእለቱ አዲስ መልስ እየተሰጠባቸው እና አዲስ ጥያቄ እየፈጠሩ አንድ እና ወጥ መግለጫ ሳያገኙ ቀጥለዋል፡፡ ነገር ግን እነዚህን ጥያቄዎች ጠቅለል አድርጎ ይገልፅልናል የምንለው የአሜሪካው 16ኛ ፕሬዘደንት፣ አብርሃም ሊንከን ታዋቂውን የጌትስበርግ ንግግራቸውን ያጠቃለሉበት “[…] that government of the people, by the people, for the people, shall not perish from the earth.” የተባለው ሀሳብ ነው፡፡ ከሕዝብ ለሕዝብ፣ በሕዝብ የሆነውን ስርዓትም ዘመናዊ ፀሃፍት ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንደሆነ እና የዴሞክራሲ ምንጯ ሕዝብ፤ ጠላቷም የሕዝብ ጠላት እንደሆኑ ይተነትናሉ፡፡

ጫትና ሺሻ በአዳማ ከተማ ለሴተኛ አዳሪነት መስፋፋት ምክንያት እየሆኑ ነው ተባለ

ጫትና ሺሻ በአዳማ ከተማ ለሴተኛ አዳሪነት መስፋፋት ምክንያት እየሆኑ ነው ተባለ

 hutበአዳማ ከተማ  የጫት መሸጪያ ሱቆች በከፍተኛ ደረጃ እተስፋፉና የቃሚውም  ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው ተባለ ፡፡


መኖሪያ ቤቶችን ጨምሮ ከመለስተኛ አንስቶ እስከ አለም አቀፍ ሆቴሎች ድረስም በዚህ የጫት ማስቃምና የሺሻ ማስጨስ ተግባር ውስጥ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡


የከተማው ነዋሪዎች ልጆቻችን በዚህ ችግር ውስጥ እየወደቁ ነው በዚህ ምክንያትም ለጎዳና ተዳዳሪነት የሚዳረጉና የታዳጊ ህፃናት ሴተኛ አዳሪነትም በከተማዋ እየተስፋፋ ነው ይላሉ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጠው በማሳሰብ።በዚህ ችግር ውስጥ የአዳማ ዩንቨርስቲ ተማሪዎችም ግንባር ቀደም ተሳታፊ እየሆኑ መምጣታቸው ጉዳዩን አሳሳቢ አድርጎታል ።

ይህ የጫት አቅርቦት ጉዳይ የአዳማ ዩንቨርስቲን ጨምሮ በከተማው በሚገኙ ኮሌጆችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አቅራቢያ ጭምር በብዛት ይስተዋላል።

ባልደረባችን  በከተማዋ ተገኝቶ ባደረገው ምልከታም በአዳማ አብዛኛዎቹ ሆቴሎች  ውስጥ መቃሚያ ክፍሎችን በማዘጋጀት ለህገ-ወጥ ገቢ ማግኛ መጠቀም የተለመደ ነው።ይባስ ብሎም አንዳንድ የከተማዋ  ሆቴሎች ማስታወቂያዎችን ጭምር በመለጠፍ ማስቃሚያ ቦታ እንዳላቸው ያስተዋውቃሉ፡፡

ቡናውን የሚያፈሉና ሺሻውን ለተጠቃሚዎቹ  የሚያቀርቡት ደግሞ ታዳጊ ሴቶች ናቸው ።በተለይ አርብ ፣ቅዳሜና እሁድ  ለዚሁ ተግባር ከአዲስ አበባና ሌሎች የአቅራቢያ ከተሞች ወደ አዳማ  የሚገባው ሰው ቁጥርም ከፍተኛ ነው።ጉዳዩን አስመልክቶ  የአዳማ ከተማ አስተዳደር  ምክትል ከንቲባ አቶ አህመድ የሱፍ  ችግሩ መኖሩን አምነው፥ይህም ለከተማዋ ፀጥታ ጭምር አሳሳቢ መሆኑን ያነሳሉ ይህ ጉዳይ ከዚህ በፊት በከተማው አስፋፍቶት የነበረውን ወንጀል በማስታወስ ።


አቶ አህመድ እንደሚሉትና ህብረተሰቡም እንዳነሳው በሆቴል ቤቶች የሚቅሙት  የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞችም ጭምር ናቸው።በመሆኑም በዚህ ድርጊት ውስጥ የተገኙ ሰራተኞችን ባለፈው ወር ከስራ አግደናል ይላሉ ምክትል ከንቲባው።ይህንን  ችግር ለመፍታትም ትልልቅ ሆቴሎችን ጨምሮ የተለያዩ  ጫት በማስቃም ስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አካላትን ፈቃዳቸውን እስከመሰረዝና ከአዳማ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ መስራት የሚቻልበትን  ሁኔታ ለመጀመር እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ነው ፡፡
በብርሃኑ ወልደሰማያት

ቤቲ ከbig brother ከመባረር ተረፈች

ቤቲ ከbig brother ከመባረር ተረፈች

Tuesday, June 18, 2013

ልጁን አስገድዶ ለሦስት ዓመታት የደፈረው አባት በፅኑ እስራት ተቀጣ

ልጁን አስገድዶ ለሦስት ዓመታት የደፈረው አባት በፅኑ እስራት ተቀጣ

 -ነዋሪነቱ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 10/11 ውስጥ ነዋሪ የሆነው ሙሉጌታ ውብሸት የተባለው ግለሰብ ልጁን አስገድዶ በመድፈርና ለሦስት ዓመታት የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲፈጽምባት መቆየቱ፣ በሰውና በሰነድ ማስረጃ በመረጋገጡ በ18 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት፡፡
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሰባተኛ ወንጀል ችሎት  ባስተላለፈው የቅጣት ውሳኔ እንደገለጸው፣ ግለሰቡ የራሱን ልጅ ከሦስት ዓመታት በፊት አስገድዶ ክብረ ንፅህናዋን ገስሷል፡፡ በወቅቱ ልጅቷ የ12 ዓመት ታዳጊ ነበረች፡፡‹‹አንች እያለሽ ሌላ ሚስት አያስፈልገኝም በማለት የራሱን ልጅ እንደ ሚስት ቆጥሮ ለሦስት ዓመታት ወንጀሉን  ፈጽሞባታል፡፡ ሕፃኗ ከሦስት ዓመታት በኋላ ለወንድሟ እኔ ምን እስከምሆን ነው የምትጠብቀኝ? አባቴ ቀለበት አድርጎ እስከሚያገባኝ ነው? በማለት በጻፈችው ደብዳቤ  የወንጀለኛው አባቷ ጉድ መጋለጡን የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ያመለክታል፡፡በቤት ውስጥ ወንጀለኛው አባቷ  የሚያኖራት እንደ ሚስትና ቤት ሠራተኛ በመሆኑ፣ ‹‹እኔ ልጅህ አይደለሁም›› ብላ እስከ መጠየቅ  መድረሷን ዓቃቤ ሕግ በምስክርነት አቅርቧት ለፍርድ ቤቱ ማስረዳቷን የውሳኔ መዝገቡ ይገልጻል፡፡

በሥነ ልቦናዋ ላይ ከባድ ጉዳት እንዳደረሰባት ለፍርድ ቤቱ በሰጠችው የምስክርነት ቃል መግለጻው የውሳኔ መዝገቡ፣ አስገድዶ መድፈርና በዘመዳሞች መካከል ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸም በወንጀል ሥር ስለሚመደብ አፈጻጸሙ ከባድ ተብሎ እንዲወሰንለት ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ቅጣት ማክበጃ ሐሳብ ፍርድ ቤቱ ተቀብሎ፣ በከባድ ወንጀል ወስኖታል፡፡

በመሆኑም ወንጀለኛውን አባት በአስገድዶ መድፈር ወንጀል በ15 ዓመታት ከሦስት ወራት ፅኑ እስራት፣ በዘመዳሞች መካከል በተፈጸመ ግብረ ሥጋ ግንኙነት በሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወራት ፅኑ እስራት፣ በድምሩ በ18 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡
ወንጀለኛው ከቤተዘመድ መብቶቹና ከሕዝባዊ መብቶቹ ለሦስት ዓመታት መሻሩንም  ፍርድ ቤቱ በውሳኔው አስታውቋል፡፡ Source: Reporter

ፌዴሬሽኑ የፊፋን ክስ አመነ

ፌዴሬሽኑ የፊፋን ክስ አመነ

MTC_2545 Addis Ababa, Ethiopia
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሁለት ቢጫ ካርድ አይቶ ሳለ ሰኔ 1/2005 ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡


ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ  አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ፊፋ አሳውቆት እንደነበር ገልጿል፡፡
ሆኖም ይህ ችግር በቡድኑ ተጫዋቾችና በደጋፊዎች ላይ ያልተፈለገ የመንፈስ ጫና እንዳይፈጥር በመስጋት መረጃውን ይፋ ሳያደርግ ቆይቷል፡፡
ፌዴሬሽኑ በፈጠረው ችግር ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ እየሰጠ ነው፡፡
ተጨማሪ መረጃዎች ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ እናቀርባለን፡፡

የአባይ ጉዳይ የዛፍ ላይ እንቅልፍ የሆነባት ግብጽ እና ለስልጣን ጸብ ጫሪው ህውሃት!

የአባይ ጉዳይ የዛፍ ላይ እንቅልፍ የሆነባት ግብጽ እና ለስልጣን ጸብ ጫሪው ህውሃት!

June 18, 2013 ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ማክሰኞ ሰኔ 11 ቀን 2005 ዓ.ም. (Tuesday, June 18, 2013)

የአባይ ጉዳይ ለግብጽ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ነው። ዛፍ ላይ ሆነህ እንቅልፍ ይወስድሃል? ሸለብ እንኳን ያደርግሻል ዛፍ ላይ ሆነሽ? እነደዚያ ነው የአባይ ጉዳይ ለግብጽ። ይኽ እንቅልፍ ማጣት እና ስጋት ዛሬ የጀመረ አይደለም። ባጭሩ ልተርክ። ሪቻርድ ፓንክረስት በግብጽ የተገኙ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ክርስቶስ ከመወለዱ ከ3 ሺ አመቶች በፊት ጀመሮ የግብጽ ነጋዴዎች በእግራቸው የአባይን ወንዝ ዳርቻ ተከትለው እንዲሁም በቀይ ባህር በነፋስ በሚገፉ ጀልባዎች ዛሬ ኢትዮጵያ (ያኔ የፐንት ግዛት) በሚባለው ግዛት ውስጥ ከሚኖረው ህዝብ ጋር የንግድ ልውውጥ ማድረጋቸውን እና ግዛቱን ምድረ ታ-ኔትጄሩ (Land Ta-Netjeru) ማለትም “ምድረ አማልዕክት” እንደሚሉት እና “የመጀመሪያ አገራችን ነው” ይሉም እንደነበር የኢትዮጵያውያን ድንበር-መሬቶች (The Ethiopian Borderlands) በሚለው መጽሐፉ ዘርዘር አድርጎ ጽፏል። የቅርቡን ብንመለከት ደግሞ በተለይ ከ1813 ዓ. ም. ጀመሮ ግብጽ የኢትዮጵያ ባለቤትነቷን በጦርነት ለማረጋገጥ የዮሐንስን ኢትዮጵያ ከሱዳን ቀላቅላ ለመግዛት በአራት አቅጣጫዎች ወረራዎች ከፍታ ሳይሳካለት ወደ መጣችበት መመለሷን ተክለ ጻዲቅ መኩሪያ “ዐፄ ዮሐንስ እና የኢትዮጵያ አንድነት በሚለው መጽሐፉ በሰፊው ተርኳል። በኃይለስላሴ እና በደርግ ዘመንም ለኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች የጦር መሳሪያ እና ስልጠና በማቀነባበር፣ ገንዘብ በመለገስ፣ በመካከለኛው ምስራቅ አረብ አገሮችን በማስተባበር፣ የአማርኛ ስርጭት ሬዲዮ በመክፈት ድጋፍ ማድረጓን እናውቃለን። ህውሃት ከተጠቃሚዎቹ ተቃዋሚዎች ውስጥ አንዱ ነው። በአባይ ጉዳይ ከጥንት ጀምሮ ግብጽ ከስጋት ነፃ የሆነ እንቅልፍ የለታም። ዛሬም ሆነ ወደፊት ግብጽ የሰላሙን መንገድ ትታ የጸበኛነቱን መንገድ ከመረጠች እንቅልፍ አይኖራትም። ይኽን የግብጽ ጭነቀት እና ስጋት ህውሃት ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህ ግንቦት 20 ቀን ጸብ ጫረ። ላብራራ።

የቢሮ ኃላፊው በሙስና ላይ ምስክር ሳይሆኑ ተገደሉ

የቢሮ ኃላፊው በሙስና ላይ ምስክር ሳይሆኑ ተገደሉ

“ብዙ ሳይታወቅ የተገደሉ ተስፋዬዎች አሉ”
food
በነበራቸው የስራ ሃላፊነት በድብቅ መረጃ ሲያሰባስቡ ቆይተው ለመንግስት ካጋለጡ በኋላ ራሳቸውን ደብቀው የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኢሬሣ ምሳ እየተመገቡ ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ። አቶ ተስፋዬ ሰኞ ለጸረ ሙስና ኮሚሽን የምስክርነት ቃላቸውን ለመስጠት ከኮሚሽነር አሊ ሱሌማን ጋር ቀጠሮ ይዘው ነበር።

በቡድናችን ድል ደስታቸውን ለመግለጽ አደባባይ ከወጡት መካከል መኪና ተገልብጦ ሁለት ሰዎች ሞቱ

በቡድናችን ድል ደስታቸውን ለመግለጽ አደባባይ ከወጡት መካከል መኪና ተገልብጦ ሁለት ሰዎች ሞቱ

BAHRDAR-SEW-MOTE.jpg (2048×1536) በባህርዳር ከተማ በብሄራዊ ቡድናችን ድል ደስታቸውን ለመግለጽ አደባባይ ከወጡት መካከል በአንድ መኪና ላይ ደስታቸውን ሆነው ሲገልጹ ከነበሩ ወገኖቻችን መካከል 2ቱ ሕይወታቸው ሊያልፍ መቻሉ ተዘገበ። በሌላ በኩልም – ኢትዮጵያ ትናንት ደቡብ አፍሪካን ማሸነፉዋን ተከትሎ ምሽት ላይ በነቂስ ወደ አደባባይ ወጥተው ድጋፍ ካደረጉት የባህር ዳር ነዋሪዎች መካከል በዛ ያለ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች “የኮከብ ዓርማ የሌለውን ሰንደቅ ዓላማ በመልበሳቸው፣ እንዲሁም ‹‹ሰማያዊ ፤ሰማያዊ ደገመው ዋልያዊ››፣ “ኢትዮጵያዊው ለሰንደቅ አላማው ፤ለሰማያዊው ” እያሉ ደስታቸውን በመግለጻቸው፣ ከፌደራል ፖሊሶች ጋር ውዝግብ ውስጥ ገብተው ማምሸታቸውን የኢሳት ቲቪ በዛሬ ምሽት የዜና እወጃው ዘገቧል።
 


ፖሊሶች ሰንደቅ ዓላማውን ለመንጠቅ ባደረጉት ሙከራ አንዳንድ ወጣቶችን መደብደባቸውን የዘገበው ኢሳት ወጣቶችም “ለባንዴራችን እንሞታለን” እያሉ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ አራት ወጣቶች ክፉኛ መደብደባቸውን የገለጸው የባህርዳሩ ወኪላችን፣ ‹‹ ፌደራል የፓርቲ ቅጥረኛ ገዳይ ነው፤ ፤የወንድሞቻችን ደም ፈሶ አይቀርም” በማለት አስፓልት ላይ ቆመው ሲናገሩ ተደምጠዋል ሲል ዘጋቢዎቹን ጠቅሶ ዘግቧል።


በግርግሩ መሀል አንድ ሚኒባስ በመገልበጡ ሁለት ወጣቶች ሲሞቱ 4 ደግሞ መቁሰላቸውን የገለጸው ቲቪው የባህርዳር ከተማ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑት ኢንስፔክተር ኢሳ ሁለት ወጣቶች መሞታቸውን ቢያምኑም ከሰንደቃላማ ጋር በተያያዘ ከፖሊስ ጋር ተፈጠረ የተባለውን ግጭት ግን አስተባብለዋል ብሏል።

ይድረስ ለአለምነህ ዋሴ፣ የአሜሪካ « ሰይጣን» በአገራችን?

ይድረስ ለአለምነህ ዋሴ፣ የአሜሪካ « ሰይጣን» በአገራችን?

June 18, 2013 ከኢየሩሳሌም አርአያ
ዛሬ ጠዋት ከመኖሪያዬ ወጥቼ ጥቂት እንደተጓዝኩ ሁለት አሜሪካዊያን ወጣቶች ከፊት ለፊቴ ሲመጡ ተመለከትኩ። እጅ ለእጅ ተያይዘዋል…በጥንቃቄ ምስላቸውን ለማስቀረት ሞከርኩ።… ( ወንድ ከወንድ- ሴት ከሴት፣ እጅ – ለእጅ መያያዝና መተቃቀፍ ግብረ-ሰዶማዊነትን ያመለክታል በአሜሪካ)… ታዲያ ምንድነው?.. ትለኝ ይሆናል፤… ይህ «ሰይጣናዊ» የነአሜሪካ «ቁሻሻ» በአገራችን መስፋፋቱ አሳስቦኝ ነው። የ11 እና 10 አመት ታዳጊ ሕፃናት ቦሌ አካባቢ በሚገኝ ት/ቤት ዳይሬክተሩን ጨምሮ 6 አስተማሪዎች እየተፈራረቁ «ሰይጣናዊ» ድርጊት ሲፈፅሙ እንደከረሙ መስማት አያስጨንቅም?… ለትምህርት የላከው ልጅህ ያውም በአስተማሪዎች እንዲህ አይነቱ ርካሽ ተግባር ሲፈፀምበት ምን ይሰማኻል?… «14ሺህ ግብረሰዶማዊያን በኢትዮጲያ አሉ» ተብሎ በአንድ ወቅት የተነገረውን ስትሰማ ምን አልክ?…ምነው ቤቲ ላይ በረታህ?… እርግጥ ነው ቤቲ የሰራችው ከአገራችን ባህል ጋር የሚጣረስ ነው!! ይህ አያከራክርም። ግን ቤቲ አረብ አገር እንደሚሰቃዩት እህቶቻችን እጣ ቢገጥማት… ይህን ያክል ትጮህላት ነበር?… በቅርቡ አረብ አገር ቁልቁል ተዘቅዝቃ ደም እየተፋች ስትገረፍ የነበረችው (ጋዜጠኛ ዳንኤል ገዛኸኝ ለጥፎት ነበር) እህታችን ሰቆቃ የሚሳየውን ቪዲዮ አይተኸዋል?… እንኳን ልታየው ከቁም ነገር ከተኸዋል?… ከ10 አመት በፊት ሟቹ ጠ/ሚ/ር በአዲስ አበባ ያለውን ሁኔታ ሲገልፁ «ሶስት መቶ ሺህ ሴተኛ አዳሪዎች በከተማዋ አሉ» ብለው ነበር። ማን የፈጠረው ችግር ነው?… ቤቲ የዚሁ አካል አይደለችም?… ሌሎቹ አደባባይ ስላልወጡ ነው?… ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ፥ የምታገለግለው ስርአት ይህን ሁሉ ችግር እንደፈጠረ ጠፍቶህ አይደለም። በስደት ስለሚያልቁትና ስለሚሰቃዩት እህትና ወንድሞቻችን አንድም ቀን ትንፍሽ ሳትል… ቤቲ ላይ ዘመትክባት። ሃቁ ግን የኢኮኖሚ ድቀት የፈጠረው ነው!!… ስለ «ሰይጣናዊው» አደገኛ የባህል ወረርሽኝ ትንፍሽ አላልክም። ለምን?… ወገኖቼ የቱ ያስጨንቃል?…

Monday, June 17, 2013

Ethiopian Telecom Corporation or Tele-corruporation?

Ethiopian Telecom Corporation or Tele-corruporation?

June 17, 2013by Alemayehu G. Mariam
“Ethiopian Telecommunications Corporation” (ETC)
In August 1998, the World Bank (WB) issued a corruption report on Ethiopia and summarized:
In the Government’s view, the following are the major determinants of corruption: a poorly functioning legal and judicial system inconsistent with the 1994 Constitution; an overregulated bureaucracy, emphasising regulation rather than service delivery; a low-paid civil service; a new yet rudimentary government, based on a federal structure; and weak budgetary and financial control, with an outdated procurement structure, and poorly trained financial staff…
That WB report made a number of recommendations to combat corruption including, “strengthening links with civil society and the private sector to identify critical areas relating to corruption”,  “elimination of excessive regulation”, “promotion of competitive market conditions and greater transparency”, and facilitation of  “dialogue among Parliament, Civil Service, Civil Society, the Private Sector, the Media, the government, the Chamber of Commerce,  other members of the business community, and civil society on implementing the anti-corruption program and developing complementary activities.”Ethiopian Telecommunications Corporation
By 2013, the “overregulated bureaucracy” of 1998 had become even more over-regulated. Government service delivery remains abysmally poor. The “new rudimentary government” had grown tentacles that crushed and pulverized everything in its reach. The “procurement structure” across agencies had been transformed into a bottomless vortex of corruption, fraud, waste and abuse of public funds, including foreign aid and international loans. The “poorly functioning legal and judicial system” evolved to become an exquisite kangaroo court system which permits arrest and incarceration of suspects without sufficient evidence. (Ethiopia is the only country in the world where the prosecution can arrest and jail suspects indefinitely while repeatedly asking leave of court to gather evidence of guilt on the suspects!) The “poorly trained staff” evolved into a sophisticated band of official thieves and swindlers. The regime that cemented itself in power in Ethiopia since 1998 is so corrupt that its venality is arguably exceeded only by the regime of General Sani Abacha of Nigeria in the mid-1990s who, alongside his family members, associates, cronies and supporters, looted Nigeria’s coffers to the tune of over USD$16 billion.

ኢሳትን ሲመለከቱ የነበሩ 60 ሰዎች መታሰራቸው ተሰማ

ኢሳትን ሲመለከቱ የነበሩ 60 ሰዎች መታሰራቸው ተሰማ

ሰኔ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በባሌ ሮቤ እና በጎባ ከተማ በቅርቡ ኢሳትን ሲመለከቱ የተገኙ ሰዎች ገናሌ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት ውስጥ መታሰራቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
ግለሰቦቹ የተያዙት በተለያዩ ሰበቦች ቢሆንም ፍርድ ቤት ሲቀርቡ የሚቀርብባቸው ክስ ግን የተቃዋሚ ጣቢያ የሆነውን ኢሳትን ሲመለከቱ ተገኝተዋል የሚል ነው።
ከታሰሩት መካከል ወጣቶች እና አረጋውያን እንደሚገኙበት የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
የፕሬስ ነጻነት ተከብሮአል በሚባልባት ኢትዮጵያ የባሌ ሮቤ እና ጎባ ከተማ ባለስልጣናት የወሰዱት እርምጃ ተገቢ አለመሆኑንና የተያዙት ግለሰቦች እንዲፈቱ የኢሳት ማኔጅመንት ጠይቋል። ማንኛውም ዜጋ ከየትኛውም አቅጣጫ የሚመጣን መረጃ ያለምንም ተጽኖ ማግኘት እንደሚችል በህገመንግስቱ የተቀመጠ መብት መሆኑን የገለጸው ማኔጅመንቱ፣ ህበረተሰቡ አንዳንድ ባለስልጣናት አለቆቻቸውን ያስደሰቱ እየመሰላቸው በሚወስዱት እርምጃ ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ ኢሳትን መመልከቱን እንዲቀጥል  ፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትም የታሰሩ ሰዎች በአፋጣኝ እንዲፈቱ እንዲያደርግ ጠይቋል።

በሌሊት እርቃኔን ሆኜ ቀዝቅዛ ውሃ እየተደፋብኝ ምርመራ ይካሄድብኛል” – ወ/ሮ አልማዝ

በሌሊት እርቃኔን ሆኜ ቀዝቅዛ ውሃ እየተደፋብኝ ምርመራ ይካሄድብኛል” – ወ/ሮ አልማዝ

በሌሊት እርቃኔን ሆኜ ቀዝቅዛ ውሃ እየተደፋብኝ ምርመራ ይካሄድብኛል” – ወ/ሮ አልማዝ
የፀረ ሙስና ኮሚሽን ባለፈው ወር ወደ ፍ/ቤት ባቀረባቸው ተጠርጣሪዎች ላይ የጀመረውን ምርመራ እንዳላጠናቀቀ በመግለፁ፤ ለሦስተኛ ጊዜ የ14 ቀናት ቀጠሮ ተፈቅዶለት ተጠርጣሪዎች በእስር እንዲቆዩ ታዘዘ፡፡ በአምስት የምርመራ መዝገቦች የተካተቱት ከአርባ በላይ ተጠርጣሪዎች ሰሞኑን እንደገና ፍ/ቤት የቀረቡ ሲሆን፤ ከተጠርጣሪዎች አንዷ የሆኑት ወ/ሮ አልማዝ ከበደ በውድቅት ሌሊት ራቁታቸውን ቀዝቃዛ ውሃ የተደፋባቸው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ለፍ/ቤቱ ገልፀዋል፡፡ ፍ/ቤቱ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በተለያዩ መዝገቦች የቀረቡት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ነጋዴዎች፣ ትራንዚተሮችና ደላላዎች እንዲሁም የገቢዎችና ጉምሩክ ሠራተኞች የጠየቁትን የዋስትና መብት በመከልከል የምርመራ ቡዱኑና አቃቤ ህግ ለ3ኛ ጊዜ የጠየቁትን የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል፡፡ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በጠበቆቻቸው ለፍ/ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ካሁን በፊት ተጠርጣሪዎቹን የያዝኳቸው በበቂ ማስረጃ ነው ማለቱን ጠቅሰው፣ ምርመራዬን አልጨረስኩም እያለ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቅ አልነበረበትም ብለዋል፡፡
 

የቢሮ ኃላፊው በሙስና ላይ ምስክር ሳይሆኑ ተገደሉ “ብዙ ሳይታወቅ የተገደሉ ተስፋዬዎች አሉ”

የቢሮ ኃላፊው በሙስና ላይ ምስክር ሳይሆኑ ተገደሉ “ብዙ ሳይታወቅ የተገደሉ ተስፋዬዎች አሉ”

በነበራቸው የስራ ሃላፊነት በድብቅ መረጃ ሲያሰባስቡ ቆይተው ለመንግስት ካጋለጡ በኋላ ራሳቸውን ደብቀው የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኢሬሣ ምሳ እየተመገቡ ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ። አቶ ተስፋዬ ሰኞ ለጸረ ሙስና ኮሚሽን የምስክርነት ቃላቸውን ለመስጠት ከኮሚሽነር አሊ ሱሌማን ጋር ቀጠሮ ይዘው ነበር።
በቅርቡ ወደ ፌደራል መንግስት የተዛወሩት የጋምቤላ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ኡሞት ኦባንግ፣ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ አላግባብ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸውን፣ እንዲሁም በክልሉ የሚፈጸሙትን የተጭበረበሩ የበጀት አፈጻጸሞችንና ምዝበራዎችን የሚያጋልጡ ሰነዶችን በሚስጥር በማደራጀት ለኢህአዴግ ያቀረቡት አቶ ተስፋዬ አሟሟታቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አይሲሲን በዘረኝነት ከሰሱ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አይሲሲን በዘረኝነት ከሰሱ

ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይሲሲ) ከአፍሪካ ጋር አንድ ዓይነት ቋንቋ ማውራት ተስኖታል፡፡
50ኛ ዓመቱን በቅርቡ ያከበረው የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የመሪዎች ጉባዔ መጠናቀቅን አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አይሲሲን በዘረኝነት የከሰሱ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥና ከወንጀል ድርጊት ተጠያቂነት የሚያመልጡን ለመያዝ የተቋቋመ ቢሆንም፣ አፍሪካውያኑን ማደን ብቸኛ ሥራው መሆኑን ኅብረቱ እንደሚቃወም ገልጸዋል፡፡ የኅብረቱን ተቃውሞ ለተመድ ለማቅረብም መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል፡፡

Sunday, June 16, 2013

አባሎቻችንና አመራሮቻችን ላይ እየተወሰደ ያለውን ህገ-ወጥ እስርና ድብደባ በህዝባዊ ንቅናቄ እንታገለዋለን፣ እናስቆመዋለን!!!

አባሎቻችንና አመራሮቻችን ላይ እየተወሰደ ያለውን ህገ-ወጥ እስርና ድብደባ በህዝባዊ ንቅናቄ እንታገለዋለን፣ እናስቆመዋለን!!!

   

UDJ1

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)


አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ 

ፓርቲያችን አንድነት ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የሚገባቸውን ዴሞክራሲ፣ መልካም አስተዳደር፣ ፍትህ፣ ነፃነትና እኩልነት እንዲጎናፀፉ በማለም በፅናት ትግሉን ቀጥሏል፡፡ በዚህ ሂደትም ቁርጠኛ አመራሩና አባላቱ መስዋእትነት ከፍለዋል፡፡ አሁንም እየከፈሉ ይገኛሉ፡፡


በተለይም የፓርቲያችንን መዋቅር ለማፍረስ እረፍት የሌለው ገዥ ፓርቲ በክልሎች የሚገኙ አመራሮቻችንን ማሰር፣ መደብደብ፣ ማግለልና ስም እየለጠፉ ማስፈራራት ዋና ተግባሩ አድርጎ እየሰራበት ነው፡፡ አባሎቻችንና አመራሮቻችንም ሳይበገሩ በቁርጠኝነት ትግሉን በሰላማዊ መንገድ በመግፋት ላይ ይገኛሉ፡፡ ሰላማዊ ትግል የሚያስከፍለው ዋጋ ሁሉ ለመክፈል ቁርጠኝነቱም አላቸው፡፡


በየጊዜው በአባሎቻችንና አመራሮቻችን ላይ እየተወሰደ ያለው ህገ-ወጥ የሰብዓዊ መብት ገፈፋ፣ ጭካኔ የተሞላበት ግርፊያና ድብደባ እንኳን መንግስት ነኝ ከሚል አካል ቀርቶ ከጨካኝ ወንበዴ የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ይህንን ድርጊት ከመቃወም በዘለለ የህዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠር ማስቆም እንደሚገባ አጠንክረን እናምናለን፡፡ ህዝብ ላይ የሚፈፀም ግፍና በደል ሊፈታና ሊወገድ የሚችለው ግፍና በደል ባንገፈገፈው ህዝብ ተከታታይና ትርጉም ያለው ትግል ነው፡፡


በፓርቲያችን አመራሮች ከሚፈፀሙ ህገ-ወጥ የገዥው ፓርቲ ግፎች አንዱ አቶ ተገኝ ሲሳይ በተባለ የምእራብ አርማጭሆ የአንድነት ሰብሳቢ ላይ የተፈፀመው ህገ-ወጥ እስርና በታሰረበት የተፈፀመበት ከፍተኛ ድብደባ ነው፡፡  አቶ ተገኝ ሲሳይ ክስ ሳይመሰረትበት የአደራ እስረኛ ነው በሚል ከመጋቢት 17 ቀን 2005ዓ.ም ጀምሮ አፍነው በመውሰድ፤ እጁ እስከሚሰበር በመደብደብና ህክምና እንዳያገኝ በማድረጋቸው በህይወት መቆየቱ አጠያያቂ እስከሚሆንበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡


በአዲስ አበባም የወረዳ 19 ምክትል ሰብሳቢ የሆነው ወጣት ባህሩ ራህመቶ ከቤቱ ታፍኖ ተወስዶ የት እንደገባ ሳይታወቅ ከቆየ በኋላ ማዕከላዊ ይገኛል፡፡ ፓርቲያችን አመራሮችና አባላት ላይ እየተፈፀመ ያለውን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት፣ ህገ-ወጥ እስርና ድብደባ ከማውገዝም ባሻገር ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በመሆን ትግሉን እንቀጥላለን፡፡ በህዝባዊ ንቅናቄ አፈናና እስሩን እንታገላለን፡፡ ይህንንም በቅርቡ ይፋ የምናደርግ ይሆናል፡፡
ምንም ዓይነት ርምጃ ከትግል መስመራችን ፈቀቅ አያደርገንም!!!
                          አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
                                       ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም

ሁሉንም ነገር ለፖለቲካ ፍጆታ ለማዋል የቆረጠ ፓርቲ የሀገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ መጣሉ የማይቀር ነው!!!

ሁሉንም ነገር ለፖለቲካ ፍጆታ ለማዋል የቆረጠ ፓርቲ የሀገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ መጣሉ የማይቀር ነው!!!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
ከአአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
ሀገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ የታደለች፤ በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጧ ለብዙ ፈታኝ ሁኔታዎች  የተጋለጠች አገር ናት፡፡ በአንፃራዊነት ሲታይም ምንም እንኳን በተፈጥሮ ሀብት የታደለች ብትሆንም ዜጎቿ በርሃብ የሚሰቃዩባት፤ ከሞት ጋር ተጋፍጠው ስደትን የሚመርጡባት፤ በሙስና ተግጣ ያለቀች፣ መልካም አስተዳደር የናፈቃት የምታስቆጭ ሀገርም ናት፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ከራሱ ስልጣን ይልቅ የህዝብን ጥቅም የሚያስቀድም፣ ለህዝብ ጆሮ የሚሰጥ አስተዋይ መሪ አግኝታ አታውቅም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ለዘመናት ያልተፈቱ ችግሮችና በመሪዎቹ የሚፈጠሩ ችግሮች ትከሻውን ያጎበጡት የኢትዮጵያ ህዝብም ሉዓላዊነቱን ለማንምና ለምንም ሰጥቶ አያውቅም፣ ወደፊትም ሊሰጥ አይችልም፡፡  ይህም ስለሆነ ሀገራችን ሉዓላዊነቷ ሳይደፈር ለብዙ ሺ ዓመታት ቆይታለች፡፡

ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል

ህወሃት በእሱና በራሱ ጉጅሌ አባላቶቹና ሚዲያዎቹ “በአገራችን ታሪክ ያልታየ ክስሰት በዋናነት ዜጎች በአንድነት፣ ከድህነት በማውጣት በደስታ የተሞላ ህይወትን ለማምጣት የኢኮኖሚ እድገታችን እያደገ ነው ይለናል” ይህ በሬዲዮ አዲስ አበባ፣ በሬዲዮ ኢትዮጵያ እና በሬዲዮ ፋና ብቻ ነው። ይህ ውሸት እንደተጠበቀ ሆኖ አዲሱ የለውጥ ምእራፍ ደግሞ የወያኔ ቡችሎች በየጊዜው ከህወሃት መጋረጃ በስተጀርባ ያለውን የተደበቀውን እውነት ወይም ግንቦት 7 ሲል የነበረውን የሚያረጋግጡ መረጃዎችን መስማት መጀመራችን ነው።


ህወሃታዊ መነቃቃትን ለማምጣት ደካሞችንና ለሆዳቸው ያደሩ ባለስልጣናቱን ሰብስቦ ስለ እድገት ጎዳናና ኃይል የሚያመረቁ ትሩፋቶችን በሚዲያዎቹ ያስነግራል። የዜጎችን የስነ ልቦና ውድቀት በከፍተኛ ደረጃ የሚፈልገው ህወሃት ባሪያዎቹንና አገልጋዮቹን በጥቅማጥቅም በማሸነፍ እውነትን ይደብቁለት ዘንድ ሁሌም ሙከራ ያደርጋል። አንዱም ተሳክቶለት አያውቅም እንጅ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት የሆነው ህወሃትና የእነሱ ተላላኪ ወያኔዎች ጦር ሰብቀው፣ መሣሪያ ወድረውና በከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲያቸው ተጠቅመው ሀገሪቷን እና ህዝቡን ከፋፍለው በዘር ካርድ ተጫውተው የስልጣን እድሜያቸውን ማራዘም ተቀዳሚ አጀንዳቸው እንጂ መቼም ስለ ኢትዮጵያ አንድነትና እድገት አስበውም አልመውትም አይውቁም፡፡ የሶማሊያው ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ሙሃመድ የተናገረውም ይህንኑ ነው ተደጋገመ እንጂ።


ግንቦት ሰባት የትግል ቃልኪዳን የሚታደስበት ቀን ነዉ!!

ግንቦት ሰባት የትግል ቃልኪዳን የሚታደስበት ቀን ነዉ!!

ጋዜጣዊ መግለጫ
 የኢትዮጵያ ህዝብ በታሪክና በባህል ትስስሩ፤ በረጂም ግዜ አብሮ መኖር ልምዱና እንዲሁም በነፃነትና ዲሞክራሲ ትግል ምዕራፉ ዉስጥ በጋራ ያፈራቸዉና በባለቤትነት የሚጋራቸዉ የተለያዩ እሴቶች አሉት። ቆየት ያሉትንና በኩራት የሚያስፈነድቀንን የአድዋን ድል ወይም በኃዘን ስሜታችንን ሁሌም የሚቆጠቁጡዉን የሰማዕታት ቀን ትተን የአጭር ግዜ ትዉስታችንን ስንፈትሽ ፊታችን ላይ እንደ መስታወት ድቅን እያሉ እራሳችንን ከሚያሳያዩን ቀኖች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ግንቦት 7 1997 ዓም የዋለዉ ታሪካዊ ቀን ነዉ። ይህ ቀን በኢትዮጵያ ህዝብ የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ትግል ሂደት ዉስጥ የፀሐይንና የጨረቃን ያክል ገዝፎና ደምቆ የሚታይ ልዩ ቀን ነዉ። ግንቦት ሰባት 1997 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ ብሩህና የወደፊቱን አመላካች የሆነ ፍሬያማ ጉዞ ጀምሮ ፍሬዉን ከማየቱ በፊት የጀመረዉን ጉዞ እንዲያቋርጥ የተገደደበትና ለዘመናት አንገቱ ላይ አንደ ቀንበር ተጭኖበት የቆየዉን የአምባገነኖች ክፉ ጫና አዉልቆ ለመጣል ሲዘገጅ ዝግጅቱ በአጭር የተቀጨበት ጨለማና ተስፋ፤ ቁጭትና ጽናት አንድ ላይ የታዩበት ትንግርታዊ ቀን ነዉ።


ከፍተኛ የደህንነት ሹም ከስልጣን ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

ከፍተኛ የደህንነት ሹም ከስልጣን ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

June 16, 2013 ከኢየሩሳሌም አርአያ
የሕወሐት አባልና የአገር ውስጥ ደህንነት ዋና ሃላፊ አቶ ወልደስላሴ ከስልጣናቸው እንዲነሱ መደረጉን የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። ወ/ስላሴ ከስልጣን እንዲነሱ ያደረጉት የደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል። የሁለቱ ሹማምንት ፀብ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ ቆይቶ መጨረሻ መፈንዳቱ ታውቋል። በመቀሌ በተካሄደው የፓርቲው ጉባኤ አቶ ጌታቸው የፓርቲው ማ/ኮሚቴ አባል ሆነው እንዳይመረጡ ሰፊ ቅስቀሳ ሲካሂድ የቆየው ወ/ስላሴ በመጨረሻም የአባላት ምርጫ ሲካሄድ ባቀረበው ተቃውሞ ላይ «..ጌታቸው የተሰጠውን የፓርቲና መንግስታዊ ሃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ አይደለም፤ የአልሙዲ ተላላኪና አሽከር ሆኗል… የአላሙዲ አገልጋይ ሆኖዋል… ስለዚህም በማ/ኮሚቴ አባልነት መካተት የለበትም..» ሲል መናገሩን ያወሱት ምንጮቹ፣ የወ/ስላሴ ተቃውሞ ተቀባይነት ባለማግኘቱ አቶ ጌታቸው በማ/ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ መደረጉን አያይዘው ገልፀዋል።…


አንድ ብስጭት፤ ጉድ በል ሰላሌ ኢትዮጵያ አይደለህም ተባልክ…

946655_4270475898383_1063122582_nአንድ ብስጭት፤ ጉድ በል ሰላሌ ኢትዮጵያ አይደለህም ተባልክ…
አበበ ቶላ ፈይሳ እባላለሁ፡፡ አባቴ አቶ ቶላ ፈይሳ ልጅነቱን በኦሮምኛ ቋንቋ ተረት እየሰማ፤ ወጣትነቱን በኦሮምኛ ቋንቋ እያዜመ፤ ጉልምስናውን በኦሮምኛ እየፎከረ፤ እርጅናውን በኦሮምኛ እየመከረ የኖረ ኢትዮጵያዊ ነበር፡፡ አባቴ የአባት እና እናቱ ቋንቋ ኦሮምኛን አጥብቆ እንደሚወደው ያህል እኔ ልጁን እና እናት ሀገሩ ኢትዮጵያንም ከመውደድ በላይ ይወደናል፡፡


UDJ urges Ethiopia and Egypt to cease bellicosity

UDJ urges Ethiopia and Egypt to cease bellicosity

June 16, 2013ESAT News  June 15, 2013  
The Ethiopian opposition political party, Unity for Democracy and Justice (UDJ), has released a press release titled “A Party committed to use everything for political consumption, endangers a country’s sovereignty”. The Party’s presser urged Ethiopia and Egypt to cease making bellicose statements, stop spreading propaganda that could harm the people to people relations of the two countries and work for a diplomatic relation and focus on round table discussions.The Ethiopian opposition political party, Unity for Democracy and Justice (UDJ)
UDJ said Ethiopia has a natural right to use Abay River. It added both countries should stop using the Dam and the river as a means of calming down internal political tensions. It also called for the immediate start of a “national consensus”. UDJ also accused the Ethiopian government of using the damming of the River for political propaganda. The Party said, the government did not do enough diplomatic preparation before starting the Dam on Abay River, failed to conduct enough and reliable discussions and agreements with the Nile riparian countries and the government didn’t make enough military preparation to defend the Country if it was faced with a military aggression.

በአባይ ግድብ ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ማድረግ ተጀመረ

በአባይ ግድብ ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ማድረግ ተጀመረ

ሰኔ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ለኢሳት የደረሰው የደህንነት መረጃ እንዳመለከተው ከፍተኛ ወጪ የወጣባቸው  ቻይና እና ሩሲያ ሰራሽ ራዳሮች ሰሞኑን በአካባቢው ተተክለዋል።

መንግስት  ማንኛውንም አይነት ድንገተኛ የአየር ወይም የሰርጎ ገቦች ጥቃት ለመከላከል ዘመናዊ ራዳሮችን ከመትከል በተጨማሪ  የተወሰኑ የአጋዚ ክፍለ ጦር አባላት በአስችኳይ ወደ አካባቢው እንዲንቀሳቀሱ አድርጓል። በፌደራል ፖሊስ ሲደረግ የነበረው ጥበቃ በመከላከያ ሰራዊት አባላት እንዲጠናከር ያደረገው መንግስት ፣ በሻለቃ አበራ ወረታው አዛዥነት የሚመራው የምእራብ እዝ የ44ኛ ዳሎል ክፍለ ጦር አራተኛ ሪጂመንት በቤንሻንጉል እንዲቀመጥ ተወስናል።

በደቡብ ሱዳን ያለው ጦር የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲያገኝም አብዩታዊ ዴሞክራሲ እና ወታደራዊ አመራር የሚል ርእስ ያዘለ የመወያያ ጽሁፍ ተዘጋጅቶ በ ስልጠና ዋና መምሪያ. ሌ/ጅኔራል  ታደሰ ወረደ የሚመራ ቡድን ወደ አብየ አቅንቷል፡፡
ኢሳት የደረሱትን ሙሉ ወታደራዊ የደህንነት መረጃዎች ለአገር ደህንነት ሲባል ይፋ ከማውጣት መቆጠቡን ለመግለጽ ይወዳል። የኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምኦን ኢትዮጵያ ምንም አይነት ወታደራዊ ዝግጅት እያደረገች አይደለም በማለት ሰሞኑን መግለጫ ቢሰጡም፣ ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ግን ኢትዮጵያ ግድቡን ከጥቃት ለመከላከል እንቅስቃሴዎችን ጀምራለች።

በሌላ ዜና ደግሞ  የግብጽ መንግስት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ  የማሸሻያ እርምጃ እንድታደርግ መጠየቁ ታውቋል። የግብጽ መንግስት ያቀረበው ጥያቄ የግድቡ ከፍታ ከነበረበት 145 ሜትር ወደ 100 ሜትር ዝቅ እንዲል፣ 74 ቢሊዩን ሜትር ኩብ ውሃ እንደሚይዝ የሚጠበቀው አዲሱ ሀይቅ  ከ 32 እስከ  40 ቢሊዩን ሜትር ኩብ ውሀ እንዲቀንስ መጠየቁን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ የሀይል አቅርቦቱም ወደ 3000 ሜጋ ዋት እንዲቀንስ የግብጽ መንግስት ጥያቄ አቅርቧል።

በወገኖቻችን ስደት ላይ ስለሚሰማው የሰሞኑ ፌዝና ቧልት ጥቂት ስለማለት

በወገኖቻችን ስደት ላይ ስለሚሰማው የሰሞኑ ፌዝና ቧልት ጥቂት ስለማለት

June 13, 2013 ዶ/ር ዘላለም ተክሉ
በሰሞኑ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ ቀጥሎ ታላቁ የወያኔ ፕሮፓጋንዳ  ከሃገራችን በመቶ ሺዎች ተሰደው ስለሚወጡ ወገኖቻችን መሆኑ ይገነዘቧል:: ከ”መለስ ራዕይ” አስፈጻሚው “ጠ/ ሚንስትር” በተዋረድ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እንደ ገደል ማሚቶ  በሚስተጋባው ዘገባ፣ ወገኖቻችን ከአረብ ሃገራት እስከ ደቡብ አፍሪካ፣አውሮጳና አሜሪካ ድረስ ህጋዊና ህጋዊ ባልሆኑ መንገዶች ተሰደው የሚኮበልሉት “ባደገችው የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ያሉትን የስራና የንግድ ዕድሎች አሟጠው ሳይገነዘቡና ሳይሞክሩ” እንደሆነ እየተነገረ መሆኑ ሁላችንን እያስስገረመን እያስደመመን ይገኛል::

ከፍተኛ የደህንነት ሹም ከስልጣን ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

ከፍተኛ የደህንነት ሹም ከስልጣን ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

Posted: June 16, 2013 in Amharic News
0
11 የሕወሐት አባልና የአገር ውስጥ ደህንነት ዋና ሃላፊ አቶ ወልደስላሴ ከስልጣናቸው እንዲነሱ መደረጉን የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። ወ/ስላሴ ከስልጣን እንዲነሱ ያደረጉት የደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል። የሁለቱ ሹማምንት ፀብ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ ቆይቶ መጨረሻ መፈንዳቱ ታውቋል። በመቀሌ በተካሄደው የፓርቲው ጉባኤ አቶ ጌታቸው የፓርቲው ማ/ኮሚቴ አባል ሆነው እንዳይመረጡ ሰፊ ቅስቀሳ ሲካሂድ የቆየው ወ/ስላሴ በመጨረሻም የአባላት ምርጫ ሲካሄድ ባቀረበው ተቃውሞ ላይ « ..ጌታቸው የተሰጠውን የፓርቲና መንግስታዊ ሃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ አይደለም፤ የአልሙዲ ተላላኪና አሽከር ሆኗል…የአላሙዲ አገልጋይ ሆኖዋል…ስለዚህም በማ/ኮሚቴ አባልነት መካተት የለበትም..» ሲል መናገሩን ያወሱት ምንጮቹ፣ የወ/ስላሴ ተቃውሞ ተቀባይነት ባለማግኘቱ አቶ ጌታቸው በማ/ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ መደረጉን አያይዘው ገልፀዋል። ..
አቶ ጌታቸው በቅርቡ በወሰዱት የአፀፋ እርምጃ ወ/ስላሴ ከአገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊነታቸው እንዲነሱ በማድረግ እንደተበቀሏቸው ማወቅ ተችሏል። በጎንደር ተወልደው ያደጉትና በሰባዎቹ መጀመሪያ አመታት ሕወሐትን የተቀላቀሉት አቶ ጌታቸው በአብዛኛው አመራር « ጥሩ ሰው ነው፣ ላመነበት ነገር ወደኋላ የማያፈገፍግ..» ተብሎ እንደሚነገርላቸው ምንጮቹ ጠቁመዋል። በሟቹ የደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ተተክተው በ1994ዓ.ም ወደስልጣን የመጡት ጌታቸው በተጨባጭ ሙስና ፈፅመዋል የሚል መረጃ እንደሌለ ያመለከቱት ምንጮቹ ነገር ግን በአብዛኛው ባለስልጣናት የሚፈፀመው መጠነ ሰፊ ዘረፋና ሙስና በተመለከተ በርካታ መረጃና ማስረጃ በጌታቸው እጅ እንደሚገኝ አያይዘው ገለፀዋል። በሌላም በኩል በ1994ዓ.ም በደህንነት ቢሮ የበታች ሹማምንት ሆነው በአቶ መለስ ከተመደቡት መካከል ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስና ወ/ስላሴ እንደሚገኙበት ያስታወሱት ምንጮቹ፣ አክለውም ሁለቱ የሕወሐት አባላት ከስር ሆነው ፈላጭ ቆራጭ አመራር ይሰጡ እንደነበረና በዚህ ተግባራቸው ከጌታቸው ጋር የከረረ ውዝግብ ውስጥ ገብተው መቆየታቸውን አስታውቀዋል። ኢሳያስ ከአቶ መለስና ስብሃት ጋር ስጋ ዝምድና እንዳለው ማወቅ ተችሏል። በተለይም በዚህ ጣልቃ ገብ አሰራር ተማረው የቆዩት አቶ ጌታቸው ከቅርብ አመት ወዲህ ከአቶ መለስ ጋር ጭምር አለመግባባት ፈጥረው እንደነበረ ሲታወቅ፣ አቶ መለስ የጤና ችግር ተፈጥሮቦቻው እንጂ በዛው ወቅት ከስልጣን ሊያነሷቸው ከወሰኑት ባለስልጣናት አንዱ ጌታቸው እንደነበሩና ከመለስ ህልፈት በኋላ የደህንነቱ ሹም የታቀደባቸውን እንደደረሱበት ምንጮቹ አስታውቀዋል። የጠ/ሚ/ሩን ህልፈት ተከትሎም አቶ ጌታቸው ስልጣናቸውን በማደላደል ጎልተው መውጣቸውንና በወ/ስላሴ ላይ የወሰዱት እርምጃ ማስረጃ እንደሆነ አያይዘው ገልፀዋል። ከዚህ በተጨማሪ የአቶ ጌታቸው ወንድም ዳንኤል አሰፋ የሕወሐት ማ/ኮሚቴ አባል ተደርጎ ባለፈው ጉባኤ መመረጡ ሲታወቅ፣ የዳንኤል ባለቤት የስብሃት ነጋ ዘመድ እንደሆነች ተጠቁሞዋል።
 

አቶ ጌታቸው በቅርቡ በወሰዱት የአፀፋ እርምጃ ወ/ስላሴ ከአገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊነታቸው እንዲነሱ በማድረግ እንደተበቀሏቸው ማወቅ ተችሏል። በጎንደር ተወልደው ያደጉትና በሰባዎቹ መጀመሪያ አመታት ሕወሐትን የተቀላቀሉት አቶ ጌታቸው በአብዛኛው አመራር « ጥሩ ሰው ነው፣ ላመነበት ነገር ወደኋላ የማያፈገፍግ..» ተብሎ እንደሚነገርላቸው ምንጮቹ ጠቁመዋል። በሟቹ የደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ተተክተው በ1994ዓ.ም ወደስልጣን የመጡት ጌታቸው በተጨባጭ ሙስና ፈፅመዋል የሚል መረጃ እንደሌለ ያመለከቱት ምንጮቹ ነገር ግን በአብዛኛው ባለስልጣናት የሚፈፀመው መጠነ ሰፊ ዘረፋና ሙስና በተመለከተ በርካታ መረጃና ማስረጃ በጌታቸው እጅ እንደሚገኝ አያይዘው ገለፀዋል። በሌላም በኩል በ1994ዓ.ም በደህንነት ቢሮ የበታች ሹማምንት ሆነው በአቶ መለስ ከተመደቡት መካከል ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስና ወ/ስላሴ እንደሚገኙበት ያስታወሱት ምንጮቹ፣ አክለውም ሁለቱ የሕወሐት አባላት ከስር ሆነው ፈላጭ ቆራጭ አመራር ይሰጡ እንደነበረና በዚህ ተግባራቸው ከጌታቸው ጋር የከረረ ውዝግብ ውስጥ ገብተው መቆየታቸውን አስታውቀዋል። ኢሳያስ ከአቶ መለስና ስብሃት ጋር ስጋ ዝምድና እንዳለው ማወቅ ተችሏል። በተለይም በዚህ ጣልቃ ገብ አሰራር ተማረው የቆዩት አቶ ጌታቸው ከቅርብ አመት ወዲህ ከአቶ መለስ ጋር ጭምር አለመግባባት ፈጥረው እንደነበረ ሲታወቅ፣ አቶ መለስ የጤና ችግር ተፈጥሮቦቻው እንጂ በዛው ወቅት ከስልጣን ሊያነሷቸው ከወሰኑት ባለስልጣናት አንዱ ጌታቸው እንደነበሩና ከመለስ ህልፈት በኋላ የደህንነቱ ሹም የታቀደባቸውን እንደደረሱበት ምንጮቹ አስታውቀዋል። የጠ/ሚ/ሩን ህልፈት ተከትሎም አቶ ጌታቸው ስልጣናቸውን በማደላደል ጎልተው መውጣቸውንና በወ/ስላሴ ላይ የወሰዱት እርምጃ ማስረጃ እንደሆነ አያይዘው ገልፀዋል። ከዚህ በተጨማሪ የአቶ ጌታቸው ወንድም ዳንኤል አሰፋ የሕወሐት ማ/ኮሚቴ አባል ተደርጎ ባለፈው ጉባኤ መመረጡ ሲታወቅ፣ የዳንኤል ባለቤት የስብሃት ነጋ ዘመድ እንደሆነች ተጠቁሞዋል።