Friday, September 28, 2012

የጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሣለኝ ልዩ ቃለ-ምልልስ ከቪኦኤ ጋር

አቶ ኃይለማርያም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው መንበረ መራሂ መንግሥቱን ከተረከቡ ወዲህ ለውጭ መገናኛ ብዙኃን አካል ቃለምልልስ ሲሰጡ ይህ ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ የሰጡት ልዩ ቃለ-ምልልስ የመጀመሪያቸው ነው፡፡

በኢትዮጵያ የሃገር ውስጥ ጉዳዮቿ፣ በውጭ ፖሊሲዋና እንቅስቃሴዎቿ ላይ ያነጋገራቸው የቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት ኃላፊ ፒተር ኃይንላይን ለአቶ ኃይለማርያም ካቀረባቸው ጥያቄዎች አንዱ ኢሕአዴግ የሕወሓት ተፅዕኖ እንዳለበት ይነገራል - የሚል ነበር፡፡

በመተማ ከአቶ መለስ ሞት ጋር በተያያዘ ከ120 በላይ ሰዎች ታሰሩ

ኢሳት ዜና:-ኢሳት እንዳረጋገጠው በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ደስታችሁን ገልጣችሁዋል የተባሉ ከ120 በላይ ሰዎች ታስረው ስቃይ እየደረሰባቸው ነው።

የመተማ አካባቢ ነዋሪዎች   እንደገለጡት አቶ መለስ ዜናዊ ሞታቸው እንደተሰማ ” መለስ እንኳንም ሞተ፣ ተገላገልን” በማለት በመጠጥ ቤቶች ውስጥም ሆነ በተለያዩ ቦታዎች ደስታቸውን ገልጠዋል የተባሉ ከ120 በላይ ሰዎች ታስረዋል።

ሰለ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ያልተባሉና ያልተነገሩ ነገሮች በቀድሞ ተማሪያቸው እይታ

I. መግቢያ፡-
የጠቅላይ ሚንስተር አቶ መለስ ዜናዊ ድንገተኛ ሞት ተከትሎ የአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ያልተጠበቀና ያልታሰበ ወደስልጣን መምጣት ብዙዎችን ያስገረመ ጉዳይ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ የዚች ሃገር  ጉዳይ  ያገባኛል ያሉ ብዙ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማሀበራት እና ሌሎችም የሳቸው ሹመት ለሃገሪቱ ጥሩ አጋጣሚ ሊሆን እንደሚችልና ምናልባትም ፈጣሪ ለዚች ሃገር ለውጥ ያስቀመጣቸው ሊሆኑ ሁሉ እንደሚችሉ ተስፋ አድርገውባቸዋል፡፡ እኔም ከነዚህ ወገኖች አንዱ ነኝ፡፡


ስለ ጠቅላይ ሚንስተር ኃይለማርያም ደሳለኝ በተለያዩ ድህረገጾችና ጋዜጦች ብዙ የተባሉና የተጻፉ ሲሆን አብዛኞቹ የሳቸውን በጎና ጥሩ ጎኖች የሚዳሰሱ ናቸው፡፡ ከዚህም መካከል ሰውየውን ጥሩ ሃይማኖተኛና፣ ፈርሀ እግዚአብሔር ያላቸው፣ የመልካም ስነምግባር ባለቤት፣ ቅንና ተንኮል የሌለባቸው፣ ጥሩ አስተማሪና አስተዳዳሪ የነበሩ፣ ቤተሰባቸውን የሚወዱና የሚያከብሩ፣ ሰውን የማይጎዱ፣ ምንም አይነት ሱስ የሌለባቸውና ሙስናን የሚጸየፉ ወዘተ… የሚሉ ናቸው፡፡ እኔም ከሞላ ጎደል በነዚህ የሰውየው ባህሪያቶች እና ገለጻዎች እስማማለሁ፡፡

የወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት ባልታወቀ ምክንያት ተቃጠለ

በአማራ ክልላዊ መንግስት ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ የአስተዳደሩ ጽ/ቤት መቃጠሉን የዜና ምንጮቻችን አስታወቁ፡፡ ምንጮቻችን “ነሐሴ 27/ 2004 ዓ.ም ሌሊት የአስተዳደሩ ጽ/ቤት ተቃጥሎአል” ብለዋል፡፡