Thursday, July 4, 2013

እስቲ እንግጠም፤ …እኛ እና ግብጥ

እስቲ እንግጠም፤ …እኛ እና ግብጥ

1010974_10151763684398690_1412303939_nእስቲ እንግጠም፤ …እኛ እና ግብጥ
እኛ…
ሃያ ሁለት አመት አንዱን ብቻ ለብሰን
ከላያችን አድፎ እንኳን መቀየሩ፤ ማፅዳት ሲቸግረን
የግብጥ ጎረምሶች እጅጉን ዘነጡ
በሁለት አመት ውስጥ ሁለቱን ለወጡ
ከዘነጡም ይልቅ፤
እጅግ ተቀናጡ
አረ ከዛም በላይ፤
እጅጉን ቀበጡ
እንዲህ ያረጋቸው ምን ይሆን መጠጡ…
ጡ…
ጡ…
ጡ…
(ግብጦ ጠጥተው ነው ያልከኝ ልጅ ግብጦ እኮ የኛ መጠጥ ነው… ሞቅ እንኳ አላደርግ አለን እንጂ… ልሳቅ ወይስ ልተወው… አለ ጥርሴ! (ማን ነበርክ አቤ አንተ እና ግጥም አልተገጣጠማችሁም ያልከኝ… ሰውን ሰው ያደረገው አስተያየት ነው ብዬ ሂስህን ተቀብዬዋለሁ፡፡ መግጠሜን ግን አቀጥላለሁ… መጋጠም ቢያቅተን መግጠም ምናባቱ!))

ትምህርት ሚኒስቴርነት፤ በማማረር ወይስ በማባረር…! ?

ትምህርት ሚኒስቴርነት፤ በማማረር ወይስ በማባረር…! ?

south_president (1)ትምህርት ሚኒስቴርነት፤ በማማረር ወይስ በማባረር…! ?
መንጌ የነገረኝ ቀልድ ትቅደም፤
መንጌ ማለት አሉኝ ከምላቸው ጓደኞቼ ውስጥ አንዱ ነው፡፡ እሳት የላሰ የአራዳ ልጅ ነው፡፡ “ካራዳ ልጅ ጋራ አብረው ቢሰደዱ፤ ባይበሉም ባይጠጡ ስንቅ ይሆናል ቀልዱ”  የተባለለት ጨዋታ አዋቂ!
አንድ ሙዝ ነጋዴ ነበር አለኝ መንጌ…
እሺ…
ሙዙ ገበያ ሲያጣ ምን ያደርጋል መሰለህ…
እ…

Monday, July 1, 2013

የአሜሪካ አዲስ ፖሊሲ በአፍሪካ ላይ …

የአሜሪካ አዲስ ፖሊሲ በአፍሪካ ላይ …

አንዲት ተረት፤ ባለ በቅሎው ሰውዬ!

አንዲት ተረት፤ ባለ በቅሎው ሰውዬ!

98764686_c9927a179e_zአንዲት ተረት፤ ባለ በቅሎው ሰውዬ!
ባለበቅሎው ሰውዬ በጠዋት ወጣ፤ ከልጁም ጋር ነበር፡፡ በበቅሎዋ ላይ እርሱ ተፈናጦ ልጁ ደግሞ ሉጓሟን እየሰባ ሲሄዱ ሲሄዱ ሲሄዱ… እመንገዳቸው ላይ ሰዎች አጋጠሟቸው፡፡ ሰዎቹም ክፉኛ ተቹት፡፡
እንደምን ያለው ራስ ወዳድ ነው ባካችሁ ልጁን ልጓም እያስጎተተ እርሱ በቅሎዋን ይጋልባል፡፡ አሉት፡፡

U.S. double-talking human rights in Ethiopia, again!

U.S. double-talking human rights in Ethiopia, again!
By Alemayehu G Mariam
July 1, 2013




As my readers know, I enjoy watchin’ American diplomats chillin’ out and kickin’ it with African dictators. I like watchin’ ‘em kumbaya-ing, back-pattin’ and fist bumpin’. I have trained myself to decipher their cryptic diplomatese spoken with forked tongue. I have also learned to chew on their indigestible words with a whopping spoonful of salt and pepper.

አቶ ስዬ በተመድ ተቀጠሩ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

አቶ ስዬ በተመድ ተቀጠሩ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

አቶ ስዬ አብርሃ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አሰከባሪ ተቋም ውስጥ በወታደራዊ አማካሪነት በጥሩ ደመወዝ መቀጠራቸውን ምንጮች ጠቆሙ። በሙስና ወንጀል ተከሰው ከወንድሞቻቸው ጋር ለስድስት አመት ታስረው የተፈቱት ስዬ በተፈቱ ማግስት የአሜሪካን ድምፅ ራዲዬን ጨምሮ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ « ፖለቲካ ከልጅነቴ ጥርሴን የነቀልኩበትና አብዛኛው እድሜዬን ያሳለፍኩበት በመሆኑ ከትግሉ መድረክ ልርቅ ጨርሶ አልችልም» በማለት አስረግጠው መናገራቸውን እነዚሁ ወገኖች ያስታውሳሉ። « መድረክ » የሚል የፖለቲካ ስብስብ ከፈጠሩና የአንድነት አባል መሆናቸውን በይፋ ካወጁ በኋላ «ለትምህርት» በሚል ወደ አሜሪካ የመጡት ስዬ ከአንድነት ፓርቲ ሪፖርት እንዲያደርጉ

“(ከኢትዮጵያ ጋር) በፕሬዚዳንት ደረጃ ግንኙነታችንን ማጉላት አንፈልግም”

“(ከኢትዮጵያ ጋር) በፕሬዚዳንት ደረጃ ግንኙነታችንን ማጉላት አንፈልግም”

ከመካከለኛው አፍሪካ የአሜሪካንን ቀልብ የሚስብ አገር የለም። የደቡብ አፍሪካ መመረጥ ካላት ኢኮኖሚና ፖለቲካዊ ሚናዋ አንጻር ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም ያሉት ዴቪድ ሺን ከምስራቅ አፍሪካ አስር አገሮች መካከል አራቱን በመምረጥ የግል አስተያየታቸውን አቅርበዋል። ሴኔጋል የተመረጠችው ፈረንሳይኛ ተናጋሪና የምዕራብ አፍሪካ አገር በመሆኗ ነው።


የቪኦኤው ሰለሞን አባተ ያነጋገራቸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ የቀድሞ አምባሳደር ዴቪድ ሺን ስለ ባራክ ኦባማ የአፍሪካ ጉብኝት ሲናገሩ ኬኒያን አንስተው ነበር። የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ አባት ኬንያዊ ቢሆኑም ኦባማ ኬንያን የጉብኝታቸው አካል ያላደረጉት አዲሱ ፕሬዚዳንትና ምክትላቸው በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ችሎት የሚፈለጉ በመሆናቸው እንደሆነ አስታውቀዋል። በወንጀል የሚፈለጉ መሪዎች ባሉበት አገር የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጉብኝት አያደርግም በማለት ተናግረዋል።
o in africaዩጋንዳ ፣ ኢትዮጵያና ታንዛንያን ለንጽጽር ያቀረቡት ዶ/ር ሺን ሶስቱም አገሮች አሜሪካ የምታስቀምጠውን መለኪያ አያሟሉም። በታንዛኒያ ግን የፕሬዚዳንቱ የስልጣን ጊዜ ባግባቡ ተገድቦ ተቀምጧል። የአመራር ለውጥ ያካሂዳሉ። ጎልቶ የሚወጣ የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት አያያዝ ጉድለት አይታይም ብለዋል። በዚህም የተነሳ ታንዛኒያ የተሻለች አገር ተብላ መመረጧን አመልክተዋል።

ስፖርታዊ ግልሙትና

ስፖርታዊ ግልሙትና

June 30, 2013 ከቴድሮስ ሓይሌ
ስፖርት ታላላቅ የአካልና የመንፈስ እሴቶችን ለሰው ልጆች ካበረከተው በላይ ሕዝብን በማቀራረብ ወንድማማችነት እንዲሰፍን መራራቅን በማስወገድ አብሮነትን በማጠናከር ረገድ አቻ የማይገኝለት በዓለማችን ላይ መልካም ነገር ቢኖር ስፖርት ብቻ ነው። ስፖርት በተለይ ለኛ በስደት ላለነው ለኢትዮጽያዊያን ከደረሰብን የመለያየትና የመጠፋፋት ዘመቻ በማርገብ ረገድ ያስገኘልን ጥቅም ቃላት ሊገልጸው ከሚችለው በላይ ለመሆኑ የ30 አመታቱ የሰሜን አሜሪካው ስፖርት ማህበር ጉዞ ከአባት ወደ ልጅ ትውልዳዊ ሽግግር የደረሰበትን ታሪካዊ ጉዞ መጥቀሱ ብቻ በቂ ይመስለኛል። ከዚህም በላይ በሃገር ውስጥ ያለው ወገናችን በዘር ፖለቲካው የጎሪጥ እንዲተያይ ተደርጎ በተለያየ ጽንፍ ጠርዝ ይዞ በቆየበት ባለፉት ሃያሁለት አመታት ውስጥ በጋራ በአንድ ድምጽ የቆመበት አጋጣሚ ቢኖር የአትሌቶቻችን ስፖርታዊ ድልና የብሄራዊ ቡድናችን ከ30 አመት በኋላ የተቀዳጀው ውጤት ምን ያህል የሁላችንንም ስሜት ፈንቅሎ ከዳር እዳር እንዳስፈነጠዘን የነበረውን የጦዘ ልዩነትን በማለዘብ ትከሻ ለትከሻ አስተቃቅፎ እንዳቆመን በቅርቡ ያየነው ነው።AESA ONE, corrupt Ethiopian football
ይህን አቀራራቢ የአብሮነት መዐድ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ለማዋል በሃገር ውስጥ ያለው ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ የብሄራዊ ቡድናችንን ውጤት ሳይቀር ለዛ ነብሰ ገዳይ መሪያቸው መለስ ዜናዊ መታሰቢያ ለማድረግ ያደረጉትን አሳፋሪ ተግባር ከያቅጣጫው በተነሳባቸው ተቃውሞ ቢተውትም ርካሽ አላማቸውን ለማሰራጨት የሚያደርጉትን ኢ-ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ካለማቆማቸውም በላይ ቀን ያነሳውን ተባባሪያቸው የሆነውን ከበርቴ ግለሰብ በሃገሪቱ ስፖርት ተቋማት ላይ እንደልቡ እንዲጋልብበት አጋር በመሆን እየፈጸሙ ያለውን አሳፋሪ ተግባር ወደ ባህር ማዶም በማሸጋገር ለሦስት አስዕርተ አመታት በስደተኛው ወገን ትጋትና ጥረት