Friday, June 28, 2013

አሜሪካ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፍቃድና ሰነዶች የሚኖሩ ከአሥራ አንድ ሚሊየን በላይ ሰዎችን ወደ ዜግነት ሊወስድ እንደሚችል የታመነበት የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ሕግ በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ በከፍተኛ ድምፅ አለፈ፡፡

አሜሪካ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፍቃድና ሰነዶች የሚኖሩ ከአሥራ አንድ ሚሊየን በላይ ሰዎችን ወደ ዜግነት ሊወስድ እንደሚችል የታመነበት የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ሕግ በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ በከፍተኛ ድምፅ አለፈ፡፡

C76B7AE3-8C3B-441E-A763-5A2C1034660C_w640_s
ዓርብ, ጁን 28, 2013
አሜሪካ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፍቃድና ሰነዶች የሚኖሩ ከአሥራ አንድ ሚሊየን በላይ ሰዎችን ወደ ዜግነት ሊወስድ እንደሚችል የታመነበት የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ሕግ በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ በከፍተኛ ድምፅ አለፈ፡፡ አሜሪካ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፍቃድና ሰነዶች የሚኖሩ ከአሥራ አንድ ሚሊየን በላይ ሰዎችን ወደ ዜግነት ሊወስድ እንደሚችል የታመነበት የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ሕግ በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ በከፍተኛ ድምፅ አለፈ፡፡


በምክር ቤቱ ውስጥ ዛሬ በተሰጠው ድምፅ 68 ሴናተሮች የድጋፍ ድምፃቸውን ሲሰጡ 32 ሴናተሮች ደግሞ ተቃውመውታል፡፡
ይህ ሕግ አያይዞም ዩናይትድ ስቴትስ የተጠናከረ የወሰን ጥበቃ እንዲኖራት የሚያዝዝ ሲሆን ከሜክሲኮ ጋር ባላት ድንበር ላይ ሃያ ሺህ ተጨማሪ የወሰን ቃፊሮች እንዲሠማሩ እና የአንድ ሺህ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው አዲስ አጥር እንዲሠራ ይፈቅዳል፡፡

የተበላሸውን የሃገሪቱን የኢሚግሬሽን ሥርዓት ለመጠገን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬድ ነው ሲሉ የሕጉ ደጋፊ የሆኑት በአፍሪካ ጉብኝት ላይ የሚገኙት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለዛሬው የሴኔቱ ውሣኔ አድናቆታቸውን ገልፀዋል፡፡

ሕጉ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለተወካዮች ምክር ቤቱ የሕግ መምሪያው እንደራሴዎች ለድምፅ ይቀርባል፡፡
ሕግ ለጣሱ ምህረት የሚሰጥ ነው የሚሉትን ማንኛውንም እርምጃ እንደሚቃወሙ ወግ አጥባቂ ሪፐብሊካኖች ይናገራሉ፡፡
source,,http://amharic.voanews.com/content/us-senate-passes-immigration-reform/1690849.html

No comments:

Post a Comment