Sunday, May 26, 2013

የሰበሩ ዝርዝር፤ ብራቮ ከንቲባ…. ብራቮ ሰማያዊ!!!

968802_418767841554502_16363769_nየሰበሩ ዝርዝር፤ ብራቮ ከንቲባ…. ብራቮ ሰማያዊ!!!
ለሚመለከተው አካል ማመልከቻ ቢያሰገባም ደብዳቤውን አንቀበልም የተባለው ሰማያዊ ፓርቲ በእማኞች ፊት ማመልከቻውን አስገብቶ ለከንቲባ ጽ/ቤትም አቤት ብሎ ነበር፡፡ እኛም ይህንን አስመልክቶ በጠዋቱ ዜና በጨዋታችን እንዲህ ብለን ነበር….
…..የጽ/ቤቱ ሃላፊዎች ለምን ደብዳቤውን አንቀበልም እንዳሉ እንጃላቸው… ምናልባት እነርሱም በመንግስታቸው የተከፉበት ጉዳ ይኖራል፡፡ (ይቺ የግዳጅ ቦንድ ግዢ እኮ ሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት ላይ ከባድ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ነው ያላት….) የምሬን ነውኮ… እነዚህ ሃላፊዎች በመንግስታቸው ላይ ቅሬታ ባይኖራቸው ኖሮ ደብዳቤውን ተቀብለው …
ለሰማያዊ ፓርቲ ባሉበት፤ 

Tuesday, May 21, 2013

Off Political Taboos and Woos

 

 Off Political Taboos and Woos

by Teklu Abate
The regime in Ethiopia and the opposition in the Diaspora and at home appear to live in totally different ‘worlds’. Each is a typical alien to the other. The governing party sees the opposition as powerless, incompetent, disorganized, delusional, visionless, and remnants of the past regime. The opposition, on the other hand, tend to characterize the reign of the current regime as a complete failure. Metaphorically speaking, the gap between the opposition and the regime is, with no exaggeration, as deep and long as the Great East African rift valley which dissects Ethiopia into two. This political rift must be one of the major obstacles that stands on our way to genuine or adequate democracy.Last hope for democracy in lawless Ethiopia
In his papers entitled Breaking Political Barriers and Political Taboos” and “Better to Light a Candle than Curse the Darkness» (both published in different times at EthioMedia), Professor Tecola Hagos (henceforth Tecola, just for simplicity) makes a passionate call to all interested to enter into some sort of discourse on several seminal issues related to Ethiopian politics. The themes raised are comprehensive, significant, and timely. The overall message of the papers that the opposition/Diaspora and the regime in power should enter into discourse seems theoretically intelligible and appealing to everybody concerned about politics in Ethiopia.
 

ታሪክን የኋሊት፤ የአቶ መለስ ድንጋጤ!

e18aa0e189a0e189a0-e18c88e1888be18b8d-2እንግዲህ ይህ ከሆነ አመቱ ሆነ አይደለ… ቅዳሜም ቅዳሜ፣ እሁድም እሁድ ነው እና ምናልባት ካልተገናኘን… እንዳንረሳው፤ ከወዲሁ ቀኑን እንደሚከተለው እንዘክረው… (በቅንፍም ኤድያ እነ እንትናዬ ደግሞ ሊበሳጩብኝ ነው… (በሌላ ቅንፍ እንግዲህ ይቻሉት እኛ ስንቱን ችለነው የለ…))

እኔ እኮ የምለው ሰው አይኑ እያየ የሰራውን ስራ እያወቀ ወደ አሜሪካ ለዛውም ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ይሄዳል እንዴ!? እውነቱን ለመናገር እኔ አቶ መለስ ዜናዊን ብሆን ኖሮ ዲቪ እንኳ ቢደርሰኝ ሀገር ይቀየርልኝ እላለሁ እንጂ አሜሪካ አልሄድም። እነ ቻይና ባሉበት አለም እነ ሰሜን ኮሪያ በሚኖሩበት ምድር ሰው እንዴት ወደ አሜሪካ ይሄዳል? (ይቅርታ ሰው በሚል የተጠቀሱት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ነው)

Thursday, May 16, 2013

ልቅ የሆነ የሙስና ግንኙነት…

melaku_fenta
ልቅ የሆነ የሙስና ግንኙነት… (ትንሽ ወግ)
አቶ መላኩ ፈንታ መንግስት የሚያውቀው በሽታ አለብኝ እና በዋስ ልፈታ፤ አሉ አሉ፤…
እኔ ደግሞ እንዲህ አልኩ፤
ምን ነካዎ አቶ መላኩ፤ መንግስት በሚያውቀው በሽታዎ ነውኮ ዘብጥያ የወረዱት፤ እርግጥ ነው ይህንን በሽታ ከየትም አላመጡትም፤ ከመንግስትዎ ጋር ባደረጉት ጥንቃቄ የጎደለው እና ልቅ የሆነ የሙስና ግንኙነት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ እርግጥ ነው መንግስታችን ራሱም የዚህ በሽታ ተጠቂ መሆኑ እሙን ነው፡፡ እርግጥ ነው በማራዘሚያ ብዛት እንጂ ሁሉም ባለስልጣኖቸች የዚህ ህመም ሰለባ መሆናቸውም ግልጽ ነው፡፡

Wednesday, May 15, 2013

ዲያስፖራው አምርሯል!

ዲያስፖራው አምርሯል!

ዲያስፖራው አምርሯል!

መንግስታችን ለአመት በዓል መዋያ ነው መሰል ሰሞኑን በየሀገራቱ እርጥባን የሚጠይቁ ሰዎችን አሰማርቷል፡፡ አብዛኛዎቹ ቦታዎችም …እግዜርም የስራህን ይስጥህ እኛ ግን የምንሰጥህ የለንም… ብለው እያባረሩት ነው…! ትላንት በኖርዌይ ኦስሎ ለሁለተኛ ጊዜ እንዲሁም ዛሬ ደግሞ በሳንዲያጎ ደጅ ጥናት የሄዱ የኢህአዴግ ባለስልታናትን ክፍ ብለዋቸዋል፡፡ ዲያስፖራው አምርሯል! መንግስታችን ግን… ልመና ይቁም…  የሚለን ዘርፉን ብቻውን መቆጣጠር ፈልጎ ነው እንዴ…!?

ማመልከቻ፤ ኢህአዴግ እንድትታሰር ስለመጠየቅ

eprdf-logoእኔ አመልካች ስሜ ከበስተመጨረሻ ባይገለፅም ግድ የለም፤ የማመለክተው ፍሬ ሀሳብ ከዚህ እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ ኢህአዴግ የተባለች የአራት ጥምር ፓርቲዎች ግንባር እንዳለች ይታወቃል፡፡ ግንባሯ ስሟ ግንባር ሲሏት ትንሽ ትመስላለች እንጂ በተለይ ሀብት ንብረቷን እንቁጠረው ብንል ማለቂያም የለው እና ግንባር ብቻ ሳትሆን ፊት፤ ፊት ብቻም ሳትሆን ጀርባ፤ ጀርባ ብቻም ሳትሆን ዳሌ ናት እንጂ ግንባር የሚለው ብቻ አይበቃትም፡፡ (በቅንፍም ለወደፊትም “ኢህአዴግ” የሚለው ስሟ አይስተካከላትምና  ”ኢህአዴዳ” ብትባል የሚል ሀሳብም አለኝ)
ለማንኛውም ግንባሪቱ፤ የሞጃዎች ሞጃ፤ የባለጠጎች ባለጠጋ፤ የቱጃሮት ቱጃር ናት፡፡

የባህር ዳሩ ገዳይ ጉዳይ፤ ኮስተር ያለ ወሬ

የባህር ዳሩ ገዳይ ጉዳይ፤ ኮስተር ያለ ወሬ

935211_10151657933187065_2091855276_nየፌስ ቡክ ወዳጆቼን ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና የኢትዮጵያ መንግስት የባህር ዳር ግድያን አስመልክቶ ምን ብለው ይሆን… የሚለውን ጠይቄ ነበር፡፡ ብዙዎቹ ያመለጠኝን ሲነግሩኝ ሌሎቹም ደግሞ በቀጣይ ኢቲቪ በጉዳዩ ላይ ሊያወራ የያዘውን ቀጠሮ ነገሩኝ፤ እኔም አድብቼ ጠብቄ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን አየሁት፤

እንደተለመደው ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሆነ የማጭበርበር ነገር ይታይበታል፡፡ ለምሳሌ የገዳዩ አስከሬን ከአባይ ወንዝ ውስጥ ሰጥሞ በመከራ ነው ያገኘነው ሲሉ አሰማን፡፡ የገዳዩን ፎቶ እንዳየነው ግን ውሃ የነካውም አይመስልም፡፡ ታድያ ጋዜጠኛው… ማንም ሊጠይቅ የሚችለውን ጥያቄ መግለጫ የሚሰጡትን ሰውዬ  ለምን አልጠየቀም ብለን ብንጠይቅ፤  የሆነ ማጭበርበር እንዳለ እንረዳለን፡፡

Tuesday, May 14, 2013

የአንደኛ ዓመት ማስታወሻ፤ ሽቅቡም ቁልቁሉም!

ዞን ዘጠኝ እንዴት ተመሠረተ? ለምን ተመሠረተ? ለምን ዞን ዘጠኝ ተባለ?… እና ሌሎችም ተመሳሳይ ጥያቄዎች ባሳለፍነው ዓመት በዞን ዘጠኝ የፌስቡክ ገጽ በብዛት ያስተናገድናቸው ጥያቄዎች ናቸው፡፡ እነሆ ‹ዞን ዘጠኝ› የሚለውን ስም አውጥተን ጦማሩን (ብሎጉን) የፈጠርንበትን ቀን (ግንቦት 5/2004) አንደኛ ዓመት በማስመልከት ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት እንሞክራለን፡፡
በሊባኖስ ቤይሩት በአሠሪዎቿ ድብደባ የደረሰባት የዓለም ደቻሳ ሞት ብዙ የማኅበራዊ አውታር ኢትዮጵያውንን አስቆጣ፡፡ ይህ ምሬት ፌስቡክን እንደማህፀን ተጠቅሞ ‘ደጉ ኢትዮጵያዊ’ የተሰኘውን ቡድን ወለደ፡፡ በአጋጣሚ የተወሰኑ የዞን ዘጠኝ አባላት እነዚህ ስብስብ ውስጥ ተገኘን፤ እንዲሁ አጋጣሚ! አንዳንዱ ለሰላምታ፣ አንዳንዱ ሲያልፍ ሲያገድም አንዱ ደግሞ የዓለም ጉዳይ አስቆጭቶት፡፡

Monday, May 13, 2013

የህዝብ አስተያየት፣ የሙስና እስርን አስመልክቶ

ሰሞኑን በወያኔዎች ቤት ብዙ ነገር እየሰማን ነው ። በተለይ ከሙስና ጋር በተያያዘ ጉዳይ ። ነገር ግን በዚህ ሙስና በሚባለው ጉዳይ የሚሰራ አንድ ድርጅት አለ ” ጸረ ሙስና ” የሚባለው ማለት ነው ። ይህ መስሪያ ቤት ከወያኔ የፋሽስት ስርዐት ለማፈንገጥ የሚሞክሩን ወይም ከዚህ የማፊያ ቡድን የተለየ ሃሳብ አመጣለሁ ለሚሉትን ወደ ከርቸሌ መወርወሪያ መስመር ነው።


ነገሩ እንዲህ ነው የወያኔ ባለስልጣን ሆኖ በሙስና ያልተዘፈቀ የለም ። ይህም መረጃ በጸረ ሙስና ቢሮ እጅ ይገኛል ። ወያኔ ማሰር ሲፈልግ በስልጣን እያሉ የተጨማለቁበትን የሙስና ጉዳይ መዘዝ በማድረግ ግለሰቦቹን ለማሸማቀቅ ብሎም ሌሎች ሙሰኞችን አድርጉ የተባሉትን ህሊናቸውን ሺጠው ህዝብን ማሰቃየትን ሳያቅማሙ እንዲቀጥሉ ለማስጠንቀቅ የተመሰረት መስሪያ ቤት ነው ።

ሰበር ዜና፣ በባህር ዳር ከተማ ከ16 በላይ ሰዎች ተገደሉ

እሁድ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ገደማ የአባይን ድልድይ እንዲጠብቅ የተመደበ የፌደራል ፖሊስ አባል እያነጣጠረ ሰዎችን ሲገድል አምሽቷል። የተለያዩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከ16-18 ንጹሀን ዜጎች ያለምንም ምክንያት ከፌደራል ፖሊሱ በተተኮሱ ጥይቶች ተገድለዋል።
የፌደራል ፖሊሱ እያነጣጠረ ንጹሀን ዜጎችን ሲገድል በአቅራቢያው የነበሩ የብአዴን ጽ/ቤት ጠባቂዎች እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥበው እንደቆዩ በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ገልጸዋል።
የብአዴን ጽ/ቤት ጠባቂዎች በግለሰቡ ላይ አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ የዜጎችን ህይወት ሊታደጉ ሲገባቸው ይልቁኑም ሰውየውን ለመያዝ በመፈለግ ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ ግለሰቡ ያገኘውን ሰው እየተኮሰ ሲገድል እንደነበር በአቅራቢያው የነበሩ ሰዎች ተናግረዋል።
ሁኔታው በባህር-ዳር ከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ መረበሽ መፍጠሩ ታውቋል። የከተማው ነዋሪዎች የሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ የተካሄደውን ኢሰብአዊ ድርጊት ለማውገዝ እንደሚፈልጉም ዜናውን ያቀበሉን የባህር-ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል።